News

National News

ዩኒቨርሲቲዎች የተሠጣቸውን ተልዕኮ በሚገባ ለይተው ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ፤ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቦንጋ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች አንድ ጊዜ ከተከፈቱ ተጠያቂነት የለም ማለት አይደለም፦ በተሠጠው ተልዕኮ መሠረት ካልሰሩ የተጠያቂነት ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባል ብለዋል።
በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች በእውነትና እውቀት ለሀገር የሚጠቅም ውይይት የሚደረግባቸው፣ ብቃት ያላቸው የሰው ሃይል ማፍራት የሚችሉ ትክክለኛ ዩኒቨርሳል የሆነ አቋም ሊኖራቸው ይገባል ለዚህም ትኩረት ተሠጥቶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስት ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች አለም አቀፍ እውቀት የሚገበይባቸው ተቋማት በመሆናቸው ተቋማዊ አሰራርን መዘርጋት ተገቢ ነው ለዚህም የዩኒቨርስቲ አመራር ምደባ በእውቀትና በአለም አቀፍ ውድድሮች ሊሆን ይገባል ያሉ ሲሆን
እንደ ሀገር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚሰራው ሥራ የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
በዩኒቨርቲው በተደረገው የሱፐርቪዥን ግኝት መሠረት ሪፖርት ያቀረቡት የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንደር አስተሳሰብ ወጥተው እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
አያይዘውም ዩኒቨርሲቲዎች በእውቀት መመራት መቻል አለባቸው ለዚህም ተቋማቱን ሪፎርም የማድረግ ሥራ እየተሰራ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
አዲሱ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲውን የተሻለ ተወዳዳሪ ለማድረግ ከዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላት ጋር በመወያየት አቅደው እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።
በመድረኩም የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላትም ከአካዳሚክ እና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንስተው በከፍተኛ አመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች አንድ ጊዜ ከተከፈቱ ተጠያቂነት የለም ማለት አይደለም፦ በተሠጠው ተልዕኮ መሠረት ካልሰሩ የተጠያቂነት ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባል ብለዋል።
በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች በእውነትና እውቀት ለሀገር የሚጠቅም ውይይት የሚደረግባቸው፣ ብቃት ያላቸው የሰው ሃይል ማፍራት የሚችሉ ትክክለኛ ዩኒቨርሳል የሆነ አቋም ሊኖራቸው ይገባል ለዚህም ትኩረት ተሠጥቶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስት ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች አለም አቀፍ እውቀት የሚገበይባቸው ተቋማት በመሆናቸው ተቋማዊ አሰራርን መዘርጋት ተገቢ ነው ለዚህም የዩኒቨርስቲ አመራር ምደባ በእውቀትና በአለም አቀፍ ውድድሮች ሊሆን ይገባል ያሉ ሲሆን
እንደ ሀገር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚሰራው ሥራ የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
በዩኒቨርቲው በተደረገው የሱፐርቪዥን ግኝት መሠረት ሪፖርት ያቀረቡት የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንደር አስተሳሰብ ወጥተው እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
አያይዘውም ዩኒቨርሲቲዎች በእውቀት መመራት መቻል አለባቸው ለዚህም ተቋማቱን ሪፎርም የማድረግ ሥራ እየተሰራ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
አዲሱ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲውን የተሻለ ተወዳዳሪ ለማድረግ ከዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላት ጋር በመወያየት አቅደው እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።
በመድረኩም የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላትም ከአካዳሚክ እና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንስተው በከፍተኛ አመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Jul 01, 2025 76
National News

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን አበረታቱ።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው የከስዓት በኋላ ፈተና አሰጣጥ ሁኔታን ተዘዋውረው በመመልከት ተፈታኝ ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱ ከሥርቆትና ኩረጃ ነፃ ለማድረግ ባለፉት ዓመታት በተሰራው ስራ ለውጥ መምጣቱን በመጥቀስ ተማሪዎች በራሳቸው በመተማመን ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ ምክር ለግሰዋል።
በኩረጃ የሚያልፍ ተማሪ ለራሱም ለሀገሩም አይበጅም ያሉት ሚኒስትሩ ከዚህ በኋላ በዚህ መንገድ የሚገኝ ውጤት አለመኖሩ ግልፅ እየሆነ መጥቷልም ብለዋል።
በዚህም ጠንክሮ ያጠናና የሰራ ተማሪ የተሻለ ውጤት እንደሚያገኝ በመግለፅ ለተማሪዎች መልካም ውጤትን ተመኝተዋል።
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከ608 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸው በወረቀትና በበየነ መረብ እንደሚወስዱ መገለፁ ይታወሳል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው የከስዓት በኋላ ፈተና አሰጣጥ ሁኔታን ተዘዋውረው በመመልከት ተፈታኝ ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱ ከሥርቆትና ኩረጃ ነፃ ለማድረግ ባለፉት ዓመታት በተሰራው ስራ ለውጥ መምጣቱን በመጥቀስ ተማሪዎች በራሳቸው በመተማመን ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ ምክር ለግሰዋል።
በኩረጃ የሚያልፍ ተማሪ ለራሱም ለሀገሩም አይበጅም ያሉት ሚኒስትሩ ከዚህ በኋላ በዚህ መንገድ የሚገኝ ውጤት አለመኖሩ ግልፅ እየሆነ መጥቷልም ብለዋል።
በዚህም ጠንክሮ ያጠናና የሰራ ተማሪ የተሻለ ውጤት እንደሚያገኝ በመግለፅ ለተማሪዎች መልካም ውጤትን ተመኝተዋል።
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከ608 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸው በወረቀትና በበየነ መረብ እንደሚወስዱ መገለፁ ይታወሳል።
Jun 30, 2025 44
National News

የ2017 ዓ.ም. 12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና በመላ አገሪቱ በይነ መረብና በወረቀት ከዛሬ ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል።

ክብርት ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ ፈተናውን በአዲስ አበባ አስጀምረዋል።፡
ክብርት የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ ከተማ እየተሰጠ የሚገኘውን ፈተና በአብርሆት ቤተ መጻህፍት ባስጀመሩበት ውቅት እንደገለጹት ለፈተናው ተገቢው የቅድመ ዝግጅት ስራ ተሰርቷል፡፡
ተማሪዎች አዲሱን ስርኣት ትምህርት መሰረት በማድረግ መጻህፍት አንድ ለአንድ እንዲደርሳቸው መደረጉን ፣ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በተዘጋጀበት አግባብም ተገቢውን እውቀት እንዲጨብጡ ጥረት መደረጉን ተናግረዋል።፡
ተማሪዎች በአግባቡ መዘጋጀት እንዲችሉና የሚገባቸውን እውቀት እንዲጨብጡ ለማድረግም ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት መሰጠቱንም ፣ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አመልክተዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር መምህራን ትርፍ ጊዜያቸውን ጭምር ተጠቅመው ተማሪዎችን ሲረዱ መቆታቸውን የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ወላጆችና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችም ተማሪዎችን ሲደግፉና ክትትል ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል።
ፈተናው በወረቅትና በበይነ መረብ እንደሚሰጥ የጠቆሙት ክረብርት ወ/ሮ አየለች በተለይ ፈተናው በበይነ መረብ መሰጠቱ ስርቆትና ኩረጃን በማስቀረት ረገድ ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም ተማሪዎች ፈተናውን በተረጋጋ ሁኑታ እንዲፈተኑና መልካም እድል እንዲገጥማቸው ተመኝተዋል፡፡
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ከዛሬ ጀምሮ በሚሰጠው ብሄራዊ ፈተና በአስተዳደሩ 280 ትምህርት ቤቶች 51 ሺ 259 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ አስታውቀዋል፡፡
የትምህርት ምዘናና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው በአገር አቀፍ ደረጃ ከ608 ሺ የሚበልጡ ተማሪዎች በወረቅትና በበይነ መረብ ፈተና እንደሚወሰዱ ጠቁመዋል፡፡
ክብርት ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ ፈተናውን በአዲስ አበባ አስጀምረዋል።፡
ክብርት የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ ከተማ እየተሰጠ የሚገኘውን ፈተና በአብርሆት ቤተ መጻህፍት ባስጀመሩበት ውቅት እንደገለጹት ለፈተናው ተገቢው የቅድመ ዝግጅት ስራ ተሰርቷል፡፡
ተማሪዎች አዲሱን ስርኣት ትምህርት መሰረት በማድረግ መጻህፍት አንድ ለአንድ እንዲደርሳቸው መደረጉን ፣ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በተዘጋጀበት አግባብም ተገቢውን እውቀት እንዲጨብጡ ጥረት መደረጉን ተናግረዋል።፡
ተማሪዎች በአግባቡ መዘጋጀት እንዲችሉና የሚገባቸውን እውቀት እንዲጨብጡ ለማድረግም ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት መሰጠቱንም ፣ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አመልክተዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር መምህራን ትርፍ ጊዜያቸውን ጭምር ተጠቅመው ተማሪዎችን ሲረዱ መቆታቸውን የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ወላጆችና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችም ተማሪዎችን ሲደግፉና ክትትል ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል።
ፈተናው በወረቅትና በበይነ መረብ እንደሚሰጥ የጠቆሙት ክረብርት ወ/ሮ አየለች በተለይ ፈተናው በበይነ መረብ መሰጠቱ ስርቆትና ኩረጃን በማስቀረት ረገድ ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም ተማሪዎች ፈተናውን በተረጋጋ ሁኑታ እንዲፈተኑና መልካም እድል እንዲገጥማቸው ተመኝተዋል፡፡
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ከዛሬ ጀምሮ በሚሰጠው ብሄራዊ ፈተና በአስተዳደሩ 280 ትምህርት ቤቶች 51 ሺ 259 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ አስታውቀዋል፡፡
የትምህርት ምዘናና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው በአገር አቀፍ ደረጃ ከ608 ሺ የሚበልጡ ተማሪዎች በወረቅትና በበይነ መረብ ፈተና እንደሚወሰዱ ጠቁመዋል፡፡
Jun 30, 2025 60
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናን በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው አስጀመሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የሚኒስቴሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ከሾጌ የ2017 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተናን በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው አስጀምረዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ጠንክሮ ያጠና ተማሪ የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በማንሳት ተማሪዎች ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ አበረታተዋል።
የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በዛሬው እለት በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
ዘንድሮ በወረቀትና በበየነ መረብ ከ608 ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሃምሌ 08/2017ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የሚኒስቴሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ከሾጌ የ2017 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተናን በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው አስጀምረዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ጠንክሮ ያጠና ተማሪ የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በማንሳት ተማሪዎች ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ አበረታተዋል።
የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በዛሬው እለት በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
ዘንድሮ በወረቀትና በበየነ መረብ ከ608 ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሃምሌ 08/2017ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል
Jun 30, 2025 70
National News

ሚኒስቴሩ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምዕራብ ኦሞ ዞን ጀሙ ከተማ የሚያስገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀመረ።

የትምህርት ቤቱን ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተጀምሯል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ትምህርት ቤት በአርብቶ አደር አካባቢ የሚገነባ መሆኑን በመጥቀስ እያንዳዱ የኢትዮጵያ ልጅ እኩል የትምህር እድል እንዲያገኝ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
ሁሉም ዜጎች አኩል እድል አግኝተው የሚማሩበት እና የበቁ፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ልጆችን ለማፍራት በሁሉም ቦታ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይጠበቃልም ብለዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማው ዘውዴ በበኩላቸው የዚህ ትምህርት ቤት ግንባታ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም ትምህርት ቤቱ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እንደ ልህቀት ማዕከል ይሆናል ያሉ ሲሆን ለአርብቶ አደሩ ልጆ ትልቅ የተስፋ መሰላል በመሆኑ ለግንባታው መጠናቀቅ አስፈለጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ሙሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን ሲሆን 537 ሚሊየን ብር ይፈጃልም ተብሏል።
ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ይህ ትምህርት ቤት በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን ወላጆች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ በመድረኩ ተጠይቋል።
ግንባታው ጥራቱን ጠብቆ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅም በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል።
የትምህርት ቤቱን ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተጀምሯል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ትምህርት ቤት በአርብቶ አደር አካባቢ የሚገነባ መሆኑን በመጥቀስ እያንዳዱ የኢትዮጵያ ልጅ እኩል የትምህር እድል እንዲያገኝ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
ሁሉም ዜጎች አኩል እድል አግኝተው የሚማሩበት እና የበቁ፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ልጆችን ለማፍራት በሁሉም ቦታ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይጠበቃልም ብለዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማው ዘውዴ በበኩላቸው የዚህ ትምህርት ቤት ግንባታ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም ትምህርት ቤቱ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እንደ ልህቀት ማዕከል ይሆናል ያሉ ሲሆን ለአርብቶ አደሩ ልጆ ትልቅ የተስፋ መሰላል በመሆኑ ለግንባታው መጠናቀቅ አስፈለጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ሙሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን ሲሆን 537 ሚሊየን ብር ይፈጃልም ተብሏል።
ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ይህ ትምህርት ቤት በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን ወላጆች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ በመድረኩ ተጠይቋል።
ግንባታው ጥራቱን ጠብቆ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅም በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል።
Jun 29, 2025 44
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁልፍ የሪፎርም ስራዎች አተገባበርና አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ጉባኤ ተካሄደ።

"አካዳሚያዊ ውይይት ለአካዳሚክ ልህቀት" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ጉባኤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንቶችና የአካዳሚክ ፕሮግራም ሀላፊዎች በቁልፍ የሪፎርም ተግባራት አፈጻጸምና አሁን ላይ ያሉበትን ደረጃ በተመለከተ ልምዳቸውን አጋርተዋል።
በትኩረትና ተልኮ መስክ ልየታ (differentiation) ፤ በሥርዓተ ትምህርት ክለሳ( Curriculum revision)፤በሠራተኞችና ተማሪዎች የሙያ እድገት (Staff and students career development)፤ በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካች መነሻና ኢላማ ልየታ ፤ KPI baseline and target identification),፣ የአፈጻጸም ኮንትራት ውል (Performance contracting implementation ) እንዲሁም በብሄራዊ ፈተናዎች አስተዳደርና አፈጻጸም ላይ የተሻለ ተሞክሮ ያላቸው ተቋማት ልምድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በቀረቡት ተሞክሮዎች ላይ ሀሳባቸውን ያካፈሉት በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኤባ ሜጄና አንዳንድ ተቋማት የሄዱበትን እርቀት አበረታተዋል።
ይሁን እንጂ በተወሠኑ ተቋማት ያለው ወጥነትና ቁርጠኝነት በሚፈለገው ልክ ባለመሆኑ ተቋማቱንም ይሁን የተቋማቱን ስራ ሀላፊዎች ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የስርዓተ ትምህርትና ፕሮግራሞች ዴስክ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ነገዎ በበኩላቸው ባቀረቡት የስራ ሪፓርት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚያከናውኑት የለውጥ ስራዎች ምቹ መደላድል የተፈጠረ መሆኑን አብራርተዋል።
አክለውም የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ እንዲሁም ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ማፍራት የሚቻለው በየደረጃው ያለው የትምህርት መዋቅር ሀላፊነቱን በሚገባ ሲወጣ በመሆኑ እዚህ ላይ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች ስር የሚገኙ የስራ ክፍሎች አፈጻጸማቸውንና ያከናወኗቸው ዋና ዋና ተግባራትን ለጉባኤው አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በመድረኩም በ2018 የትምህርት ዘመን በትኩረት መከናወን በሚገባቸው ስራዎች ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ጉባኤው ተጠናቋል።
"አካዳሚያዊ ውይይት ለአካዳሚክ ልህቀት" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ጉባኤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንቶችና የአካዳሚክ ፕሮግራም ሀላፊዎች በቁልፍ የሪፎርም ተግባራት አፈጻጸምና አሁን ላይ ያሉበትን ደረጃ በተመለከተ ልምዳቸውን አጋርተዋል።
በትኩረትና ተልኮ መስክ ልየታ (differentiation) ፤ በሥርዓተ ትምህርት ክለሳ( Curriculum revision)፤በሠራተኞችና ተማሪዎች የሙያ እድገት (Staff and students career development)፤ በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካች መነሻና ኢላማ ልየታ ፤ KPI baseline and target identification),፣ የአፈጻጸም ኮንትራት ውል (Performance contracting implementation ) እንዲሁም በብሄራዊ ፈተናዎች አስተዳደርና አፈጻጸም ላይ የተሻለ ተሞክሮ ያላቸው ተቋማት ልምድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በቀረቡት ተሞክሮዎች ላይ ሀሳባቸውን ያካፈሉት በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኤባ ሜጄና አንዳንድ ተቋማት የሄዱበትን እርቀት አበረታተዋል።
ይሁን እንጂ በተወሠኑ ተቋማት ያለው ወጥነትና ቁርጠኝነት በሚፈለገው ልክ ባለመሆኑ ተቋማቱንም ይሁን የተቋማቱን ስራ ሀላፊዎች ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የስርዓተ ትምህርትና ፕሮግራሞች ዴስክ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ነገዎ በበኩላቸው ባቀረቡት የስራ ሪፓርት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚያከናውኑት የለውጥ ስራዎች ምቹ መደላድል የተፈጠረ መሆኑን አብራርተዋል።
አክለውም የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ እንዲሁም ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ማፍራት የሚቻለው በየደረጃው ያለው የትምህርት መዋቅር ሀላፊነቱን በሚገባ ሲወጣ በመሆኑ እዚህ ላይ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች ስር የሚገኙ የስራ ክፍሎች አፈጻጸማቸውንና ያከናወኗቸው ዋና ዋና ተግባራትን ለጉባኤው አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በመድረኩም በ2018 የትምህርት ዘመን በትኩረት መከናወን በሚገባቸው ስራዎች ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ጉባኤው ተጠናቋል።
Jun 27, 2025 38
National News

ኦስትሪያ እና ኢትዮጵያ በከፍተኛ ትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ለመሥራት የሚያስችላቸውን ውይይት አካሄዱ።

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በኦስትሪያ ምክትል የፋይናንስ ሚኒስትር ‘H.E. Andreas REICHHARDT’ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ወቅት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የትምህርት ጥራትና ብቃትን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ ያሉ ሪፎርሞችን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተውላቸዋል።
በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በተልዕኮና ትኩረት መስክ በመለየት በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተው በዘርፉ የበለጠ ውጤታማ ለመሆን በትብብር የሚሰሩ ተግባራት መኖራቸውንም አብራርተዋል።
የኦስትሪያ ምክትል የፋይናን ሚኒስትር H.E. Andreas REICHHARDT በበኩላቸው ኦስትሪያና ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍ የቆየ ትብብር እንደነበራቸው አንስተው ይህንን ትብብር የበለጠ አጠናክረው መቀጠል እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የኦስትሪያ አምባሳደር ሲሞን ክናፕ ደግሞ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው የዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርስቲ ትብብርን በማጠናከር በከፍተኛ ትምህርት ልማትና በጥናትና ምርምር ዘርፍ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉም አንስተዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት በከፍተኛ ትምህርት አስተዳደር፣ በአይሲቲ ልማት እንዲሁም በምርምርና ማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይም ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በኦስትሪያ ምክትል የፋይናንስ ሚኒስትር ‘H.E. Andreas REICHHARDT’ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ወቅት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የትምህርት ጥራትና ብቃትን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ ያሉ ሪፎርሞችን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተውላቸዋል።
በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በተልዕኮና ትኩረት መስክ በመለየት በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተው በዘርፉ የበለጠ ውጤታማ ለመሆን በትብብር የሚሰሩ ተግባራት መኖራቸውንም አብራርተዋል።
የኦስትሪያ ምክትል የፋይናን ሚኒስትር H.E. Andreas REICHHARDT በበኩላቸው ኦስትሪያና ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍ የቆየ ትብብር እንደነበራቸው አንስተው ይህንን ትብብር የበለጠ አጠናክረው መቀጠል እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የኦስትሪያ አምባሳደር ሲሞን ክናፕ ደግሞ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው የዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርስቲ ትብብርን በማጠናከር በከፍተኛ ትምህርት ልማትና በጥናትና ምርምር ዘርፍ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉም አንስተዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት በከፍተኛ ትምህርት አስተዳደር፣ በአይሲቲ ልማት እንዲሁም በምርምርና ማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይም ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል።
Jun 25, 2025 32
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደርን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሻሪፍ ሚያን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ወቅት ሁለቱ አካላት በትምህርቱ ዘርፉ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዘሪያ ውይይት አድርገዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፉ እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም ለአምባሳደሩ ካብራሩ በኋላ የፓኪስታንን የትምህርት ሥርዓት እንደሚያውቁ ጠቅሰው በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ፣ በአጠቃላት ትምህርት መምህራን ስልጠና እንዲሁም በሌሎችም ዘርፎች ከፓኪስታን ጋር በጋራ መስራት እንደሚፈልጉ አንስተውላቸዋል።
በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሻሪፍ ሚያን በበኩላቸው ፓኪስታን በትምህርቱ ዘርፉ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
በተለይም ፓኪስታን በመምህራን ስልጠና፣ በሥርዓተ ትምህርት ልማት፣ በሀገራዊና እና አለም አቀፋዊ ስታንዳርድ የፈተና ዝግጅት እንዲሁም በፕሮፌሽናል ትምህርት የተሻለ ተሞክሮ እንዳላት በመጥቀስ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ መስራት በሚቻልበትን ሁኔታ አንስተዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት በትምህርቱ ዘርፍ እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ በጋር ለመስራት ተስማምተዋል።
ለዚህም ተግባራዊነት በሁለቱ አካላት መካከል በከፍተኛ ትምህርት ፕሮግራም ፣ በአጠቃላይ ትምህርት የመምህራን ስልጠና፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በህክምና ትምህርት መስክ ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ለመፈራረም ከስምምነት መደረሳቸውም በመድረኩ ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሻሪፍ ሚያን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ወቅት ሁለቱ አካላት በትምህርቱ ዘርፉ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዘሪያ ውይይት አድርገዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፉ እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም ለአምባሳደሩ ካብራሩ በኋላ የፓኪስታንን የትምህርት ሥርዓት እንደሚያውቁ ጠቅሰው በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ፣ በአጠቃላት ትምህርት መምህራን ስልጠና እንዲሁም በሌሎችም ዘርፎች ከፓኪስታን ጋር በጋራ መስራት እንደሚፈልጉ አንስተውላቸዋል።
በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሻሪፍ ሚያን በበኩላቸው ፓኪስታን በትምህርቱ ዘርፉ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
በተለይም ፓኪስታን በመምህራን ስልጠና፣ በሥርዓተ ትምህርት ልማት፣ በሀገራዊና እና አለም አቀፋዊ ስታንዳርድ የፈተና ዝግጅት እንዲሁም በፕሮፌሽናል ትምህርት የተሻለ ተሞክሮ እንዳላት በመጥቀስ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ መስራት በሚቻልበትን ሁኔታ አንስተዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት በትምህርቱ ዘርፍ እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ በጋር ለመስራት ተስማምተዋል።
ለዚህም ተግባራዊነት በሁለቱ አካላት መካከል በከፍተኛ ትምህርት ፕሮግራም ፣ በአጠቃላይ ትምህርት የመምህራን ስልጠና፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በህክምና ትምህርት መስክ ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ለመፈራረም ከስምምነት መደረሳቸውም በመድረኩ ተገልጿል።
Jun 25, 2025 28
National News

አገር አቀፍ የቅድመ ልጅነት ዕድገትና ትምህርት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ።

በንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ባለፉት ሁለት አመታት በመንግስትና በማህበረሰቡ በተሰሩ ስራዎች የቅድመ አንደኛ ትምህርትን በማስፋፋትና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ስኬቶች እየተመዘገቡ መሆኑ ተገልጿል።
"ልጆቻችን ብሩህ ነገን እንዲፈጥሩ መሠረቱን ዛሬ እንጣል " በሚል በተከናወነው መርሃ ግብር ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የሌሎች ባለድርሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ቁልፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት ላይ የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት ሊሠራበት የሚገባው ጉዳይ መሆኑን የገለጹ ሲሆን አሁን ላይ ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶችና የልማት አጋሮች ጋር በተፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የትምህርት ጥራትን በማጐልበት የሀገርን ብልጽልግና በማረጋገጥና ዜጎች ከሚመዘገበው ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ትምህርት ቁልፍ ሚና ያለው መሆኑን በመግለጽ የቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት በትምህርትና ስልጠና ፖሊሲውና በአጠቃላይ ትምህርት አዋጁ በተገቢው ሁኔታ እንዲካተት መደረጉን ያስገነዘቡት ሚንስትር ዴኤታዋ ህፃናት ጥራት ያለው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ማግኘታቸው የትምህርት ስርዓታችን ለገጠመው ስብራት መሰረታዊና ዘላቂ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን አብራርተዋል።
በዘርፉ ላይ ጠንካራ መሰረት ከተጣለ ሀገር የምትፈልገውን ዜጋ ለመቅረጽና ብሩህ የወደፊት ራዕይ ያላው ትውልድ ለመገንባትና ለማፍራት ብሎም የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የትምህርት ዘርፉ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስችለው መሆኑን አያይዘው ገልጸዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ እንደዚሁ በተመሳሳይ የትምህርት ዘርፉ ለቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት የተሰጠው ትኩረት የነገዋን ኢትዮጵያ እጣ ፋንታ የሚወስን በመሆኑ የጤና ሚኒስቴር ድጋፍና ትብብር ሁሌም የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤት መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዬሀንስ ወጋሶ በበኩላቸው ባቀረቡት ገለጻ በቅድመ ልጅነት ትምህርት ዘርፍ ቀደም ሲል የነበሩ ጉድለቶችና ክፍተቶች ዛሬ ላይ ለሚስተዋለው የተማሪዎች የትምህርት አቀባበልና ውጤታማነት ላይ አሉታዊ ተጽኖ ያለው በመሆኑ ችግሩን ከስር መሠረቱ ለመፍታት በቁርጠኝነት እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ የዩኒሴፍ ምክትል ተወካይ ማሪኮ ካጎሺማ በበኩላቸው በዘርፉ የሚከናወኑ ስራዎችን ዩኒሴፍ እንደሚደግፍ ገልጸዋል።
የቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርትን ለማስፋፋትና በተሻለ ተደራሽ ለማድረግ የትምህርት ሚኒስቴር ከክልልና ከተማ መስተዳድር ትምህርት ቢሮዎች ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል።
በንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ባለፉት ሁለት አመታት በመንግስትና በማህበረሰቡ በተሰሩ ስራዎች የቅድመ አንደኛ ትምህርትን በማስፋፋትና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ስኬቶች እየተመዘገቡ መሆኑ ተገልጿል።
"ልጆቻችን ብሩህ ነገን እንዲፈጥሩ መሠረቱን ዛሬ እንጣል " በሚል በተከናወነው መርሃ ግብር ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የሌሎች ባለድርሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ቁልፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት ላይ የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት ሊሠራበት የሚገባው ጉዳይ መሆኑን የገለጹ ሲሆን አሁን ላይ ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶችና የልማት አጋሮች ጋር በተፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የትምህርት ጥራትን በማጐልበት የሀገርን ብልጽልግና በማረጋገጥና ዜጎች ከሚመዘገበው ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ትምህርት ቁልፍ ሚና ያለው መሆኑን በመግለጽ የቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት በትምህርትና ስልጠና ፖሊሲውና በአጠቃላይ ትምህርት አዋጁ በተገቢው ሁኔታ እንዲካተት መደረጉን ያስገነዘቡት ሚንስትር ዴኤታዋ ህፃናት ጥራት ያለው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ማግኘታቸው የትምህርት ስርዓታችን ለገጠመው ስብራት መሰረታዊና ዘላቂ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን አብራርተዋል።
በዘርፉ ላይ ጠንካራ መሰረት ከተጣለ ሀገር የምትፈልገውን ዜጋ ለመቅረጽና ብሩህ የወደፊት ራዕይ ያላው ትውልድ ለመገንባትና ለማፍራት ብሎም የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የትምህርት ዘርፉ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስችለው መሆኑን አያይዘው ገልጸዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ እንደዚሁ በተመሳሳይ የትምህርት ዘርፉ ለቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት የተሰጠው ትኩረት የነገዋን ኢትዮጵያ እጣ ፋንታ የሚወስን በመሆኑ የጤና ሚኒስቴር ድጋፍና ትብብር ሁሌም የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤት መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዬሀንስ ወጋሶ በበኩላቸው ባቀረቡት ገለጻ በቅድመ ልጅነት ትምህርት ዘርፍ ቀደም ሲል የነበሩ ጉድለቶችና ክፍተቶች ዛሬ ላይ ለሚስተዋለው የተማሪዎች የትምህርት አቀባበልና ውጤታማነት ላይ አሉታዊ ተጽኖ ያለው በመሆኑ ችግሩን ከስር መሠረቱ ለመፍታት በቁርጠኝነት እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ የዩኒሴፍ ምክትል ተወካይ ማሪኮ ካጎሺማ በበኩላቸው በዘርፉ የሚከናወኑ ስራዎችን ዩኒሴፍ እንደሚደግፍ ገልጸዋል።
የቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርትን ለማስፋፋትና በተሻለ ተደራሽ ለማድረግ የትምህርት ሚኒስቴር ከክልልና ከተማ መስተዳድር ትምህርት ቢሮዎች ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል።
Jun 24, 2025 26
National News

የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ኘሮግራሞች በአገራዊው የብቃት ስታንዳርድ ተመዝነው ጥራትና ተገቢነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።

የከፍተኛ ትምህርት የአካዳሚክ ኘሮግራሞችን ጥራትና ተገቢነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጄና (ዶ/ር) ገልፀዋል ።
ከነዚህ ተግባራት መካከል የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ውጤት ተኮር (Outcome based) መርህን ተከትለው እንዲተገበሩ በትምህርትና ስልጠና ፓሊሲው ላይ በተመላከተው ድንጋጌ መሰረት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም አብራርተዋል።
የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ሥርዓተ ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ በሱፍቃድ ኃ/ማሪያም በበኩላቸው ለ37 የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የውጤት ተኮር ብቃት መለኪያ (Competency) ተዘጋጅቶ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ ሥራ መጀመሩን ገልፀዋል።
በዚህም ከ23 ዪኒቨርሲቲዎች፣ ከኢንዱስትሪዎች፣ ከሙያ ማህበራት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ የየመስኩ ባለሙያዎች በክለሳ ሥራው ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በመድረኩም የከፍተኛ ትምህርት ምሩቃንን ብቃትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል የሆነው ውጤት ተኮር (Outcome based) የትምህርት ሥርዓት ስኬታማ እንዲሆን በተለይ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለየ መልኩ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንዲወጡም ተጠይቋል።
የከፍተኛ ትምህርት የአካዳሚክ ኘሮግራሞችን ጥራትና ተገቢነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጄና (ዶ/ር) ገልፀዋል ።
ከነዚህ ተግባራት መካከል የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ውጤት ተኮር (Outcome based) መርህን ተከትለው እንዲተገበሩ በትምህርትና ስልጠና ፓሊሲው ላይ በተመላከተው ድንጋጌ መሰረት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም አብራርተዋል።
የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ሥርዓተ ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ በሱፍቃድ ኃ/ማሪያም በበኩላቸው ለ37 የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የውጤት ተኮር ብቃት መለኪያ (Competency) ተዘጋጅቶ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ ሥራ መጀመሩን ገልፀዋል።
በዚህም ከ23 ዪኒቨርሲቲዎች፣ ከኢንዱስትሪዎች፣ ከሙያ ማህበራት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ የየመስኩ ባለሙያዎች በክለሳ ሥራው ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በመድረኩም የከፍተኛ ትምህርት ምሩቃንን ብቃትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል የሆነው ውጤት ተኮር (Outcome based) የትምህርት ሥርዓት ስኬታማ እንዲሆን በተለይ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለየ መልኩ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንዲወጡም ተጠይቋል።
Jun 22, 2025 29
National News

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ተፈታኝ ተማሪዎች አበረታቱ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሺንሺቾ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ እየተሠጠ የሚገኘውን የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተዘዋውረው በመመልከት ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ምዘናና አስተዳደር ሥርዓቱን በማስተካከል ጠንክሮ በመሥራት እንጂ በሌላ መንገድ የሚገኝ ውጤት እንደሌለ ግልፅ እየሆነ መጥቷል፤
በመሆኑም ተማሪዎች ኩረጃንና ስርቆትን የሚጠየፉ መልካም ሥነ ምግባር የተላበሱ እንዲሆኑም አሳስበዋል።
አክለውም ተማሪዎች ጠንክረው በመማር በራሳቸው የሚተማመኑ ብቁና ተወዳዳሪ የነገ ሀገር ተረካቢ መሆን እንዳለባቸውም ምክር ለግሰዋል።
በተጨማሪም አመራርቹ በከንባታ ዞን በሺንሺቾ ከተማ በብራይት ቪዥን ቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ለህጻናት እየተሰጠ ያለውን ትምህርት ምልከታ አድርገዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሺንሺቾ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ እየተሠጠ የሚገኘውን የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተዘዋውረው በመመልከት ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ምዘናና አስተዳደር ሥርዓቱን በማስተካከል ጠንክሮ በመሥራት እንጂ በሌላ መንገድ የሚገኝ ውጤት እንደሌለ ግልፅ እየሆነ መጥቷል፤
በመሆኑም ተማሪዎች ኩረጃንና ስርቆትን የሚጠየፉ መልካም ሥነ ምግባር የተላበሱ እንዲሆኑም አሳስበዋል።
አክለውም ተማሪዎች ጠንክረው በመማር በራሳቸው የሚተማመኑ ብቁና ተወዳዳሪ የነገ ሀገር ተረካቢ መሆን እንዳለባቸውም ምክር ለግሰዋል።
በተጨማሪም አመራርቹ በከንባታ ዞን በሺንሺቾ ከተማ በብራይት ቪዥን ቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ለህጻናት እየተሰጠ ያለውን ትምህርት ምልከታ አድርገዋል።
Jun 13, 2025 16
National News

የመንግስት ትምህርት ቤቶች ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚገባባቸው ምቹ ተቋማት እንዲሆኑ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዱራሜ ከተማ የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተጀምሯል።
በማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓቱ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በየአካባቢው መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል።
እንደ ሀገር ከድህነት ለመውጣት ትምህርት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይገባል፤ ለዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል አግኝቶ የሚማርበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር ግዴታ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም በተፈጥሮ ያለ የኢኮኖሚ ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ በትምህርት ግን በሀብታምና ድሃ መካከል ምንም ልዩነት ሊኖር አይገባም ያሉት ሚኒስትሩ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ የሚማርበትን የመንግስት ትምህርት ቤት ተመራጭና ምቹ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የመንግስት ትምህርት ቤቶች ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚማርባቸው ተቋማት መሆን አለባቸው፤ ለዚህም አዲስ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ዲዛይን ተሠርቶ ወደ ተግባር መገባቱን ጠቅሰው ነገ የኢትዮጵያ መሪ የሚሆኑ ልጆችን ለማፍራት የሚያስችሉ ትምህርት ቤቶችን እየገነባን እንገኛለን ያሉ ሲሆን፣
ትምህርት ሚኒስቴር በመላ ሀገሪቱ በቂ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው 51 የሚደርሱ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ በበኩላቸው የትምህርት ሥርዓቱን በሁሉም ዘርፍ ለማስተካከል በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም በክልሉ አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች ከደረጃ በታች በመሆናቸው እንዲህ ዓይነት ሞዴል ትምህርት ቤቶች መገንባት ትርጉሙ ብዙነው ያሉ ሲሆን ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
ይህ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ 509 ሚሊየን ብር እንደሚፈጅና ሙሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚሸፈንም በመድረኩ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታም በአንድ ዓመት ጊዜ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ እንዲጀምር በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል ሥምምነት ተፈርሟል
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዱራሜ ከተማ የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተጀምሯል።
በማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓቱ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በየአካባቢው መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል።
እንደ ሀገር ከድህነት ለመውጣት ትምህርት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይገባል፤ ለዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል አግኝቶ የሚማርበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር ግዴታ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም በተፈጥሮ ያለ የኢኮኖሚ ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ በትምህርት ግን በሀብታምና ድሃ መካከል ምንም ልዩነት ሊኖር አይገባም ያሉት ሚኒስትሩ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ የሚማርበትን የመንግስት ትምህርት ቤት ተመራጭና ምቹ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የመንግስት ትምህርት ቤቶች ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚማርባቸው ተቋማት መሆን አለባቸው፤ ለዚህም አዲስ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ዲዛይን ተሠርቶ ወደ ተግባር መገባቱን ጠቅሰው ነገ የኢትዮጵያ መሪ የሚሆኑ ልጆችን ለማፍራት የሚያስችሉ ትምህርት ቤቶችን እየገነባን እንገኛለን ያሉ ሲሆን፣
ትምህርት ሚኒስቴር በመላ ሀገሪቱ በቂ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው 51 የሚደርሱ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ በበኩላቸው የትምህርት ሥርዓቱን በሁሉም ዘርፍ ለማስተካከል በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም በክልሉ አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች ከደረጃ በታች በመሆናቸው እንዲህ ዓይነት ሞዴል ትምህርት ቤቶች መገንባት ትርጉሙ ብዙነው ያሉ ሲሆን ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
ይህ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ 509 ሚሊየን ብር እንደሚፈጅና ሙሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚሸፈንም በመድረኩ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታም በአንድ ዓመት ጊዜ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ እንዲጀምር በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል ሥምምነት ተፈርሟል
Jun 13, 2025 19
National News

የሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራሮች የቡኢ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ ተመለከቱ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ እየተገነባ የሚገኘውን ቡኢ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ቤቱ ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ጥራቱን ጠብቆ በፍጥነት በማጠናናቀቅ በመጪው መስከረም የመጀመሪያውቹን ተማሪዎች መቀበል መጀመር አለበት ያሉ ሲሆን፤
ለዚህም ኮንትራክተሩ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀው በሚኒስቴሩ በኩል ከክፍያ ጋር የሚፈጠር ምንም አይነት መጓተት አይኖርም ብለዋል።
የፕሮጀክቱ ማናጀር እንዳለ ዘለቀ በበኩላቸው ግንባታው ጥራቱን ጠብቆ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው ሚኒስቴሩ ባስቀመጠው ጊዜ ውስጥ ተማሪዎችን ለመቀበል የሚያስችል ደረጃ ላይ ለማድረስ እየተሠራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርታቸው ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እያስገነባ እንደሚገኝም ይታወቃል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ እየተገነባ የሚገኘውን ቡኢ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ቤቱ ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ጥራቱን ጠብቆ በፍጥነት በማጠናናቀቅ በመጪው መስከረም የመጀመሪያውቹን ተማሪዎች መቀበል መጀመር አለበት ያሉ ሲሆን፤
ለዚህም ኮንትራክተሩ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀው በሚኒስቴሩ በኩል ከክፍያ ጋር የሚፈጠር ምንም አይነት መጓተት አይኖርም ብለዋል።
የፕሮጀክቱ ማናጀር እንዳለ ዘለቀ በበኩላቸው ግንባታው ጥራቱን ጠብቆ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው ሚኒስቴሩ ባስቀመጠው ጊዜ ውስጥ ተማሪዎችን ለመቀበል የሚያስችል ደረጃ ላይ ለማድረስ እየተሠራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርታቸው ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እያስገነባ እንደሚገኝም ይታወቃል።
Jun 12, 2025 16
National News

በተለያዩ የትምህርት መስክ ሰልጥነው ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ አማራጭ የአሠራር ሥርዓት ወደ ተግባር ሊገባ መሆኑ ተገለፀ። አዲስ በተዘጋጀው አማራጭ የመምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ላይ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስቴር በመምህርነት ሙያ የሚታየውን የሥልጠና እጥረት ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ሰልጥነው የሚገኙና ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ የአሠራር ሥርዓት ወደ ተግባር ሊያሰገባ መሆኑን በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ገልፀዋል።
ሀገራችን የመምህርነት ሙያ ማሰልጠን የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለት ቢሆንም አማራጭ ወደ መምህርነት ለመግባት ለሚፈልጉት አዲስ መንገድ መክፈት ያስፈልጋል፤ ለዚህም ተጨማሪ ሥልጠና ወስደው መምህር መሆን የሚችሉበት የሥልጠና ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል ብለዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ከተደረገው የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር አብሮ የሚሄድ ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው መምህራንን ለማፍራት የተለያዩ አማራጮች ተቀርፀው እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በዚህም መምህር ሆነው መሥራት ለሚፈልጉ ምሩቃን በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ገብተው ተጨማሪ የመምህርነት ሙያ፣ የሚያስተምሩት ትምህርት አይነት ይዘት ፣ የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የጋራ ኮርሶችን ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋልም ተብሏል።
የመምህራንና የትምህር አመራር ልማት ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ አሰገድ ምሬሳ በበኩላቸው የሀገራችንን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል አማራጭ የስልጠና ሞዳሊቲዎች እየተጠኑ ወደ ስራ ማስገባት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም በተደረገ የዳሰሳ ጥናት አብዛኞች በተለያዩ የትምህርት መስክ የተመረቁ ተጨማሪ የማስተማር ሙያ ስልጠና ቢሰጣቸው ወደ ሙያው የመግባት ፍላጎት እንዳለም ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
የሥልጠና ማዕቀፉን ወደ ሥራ ለማስገባትም ከአሰልጣኝ የትምህርት ተቋማት፣ ከክልል ትምህርት ቢሮና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
አዲስ የተዘጋጀው አማራጭ መምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ከቀጣይ ዓመት ጀሞሮ ወደ ተግባር ይገባልም ተብሏል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስቴር በመምህርነት ሙያ የሚታየውን የሥልጠና እጥረት ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ሰልጥነው የሚገኙና ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ የአሠራር ሥርዓት ወደ ተግባር ሊያሰገባ መሆኑን በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ገልፀዋል።
ሀገራችን የመምህርነት ሙያ ማሰልጠን የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለት ቢሆንም አማራጭ ወደ መምህርነት ለመግባት ለሚፈልጉት አዲስ መንገድ መክፈት ያስፈልጋል፤ ለዚህም ተጨማሪ ሥልጠና ወስደው መምህር መሆን የሚችሉበት የሥልጠና ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል ብለዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ከተደረገው የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር አብሮ የሚሄድ ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው መምህራንን ለማፍራት የተለያዩ አማራጮች ተቀርፀው እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በዚህም መምህር ሆነው መሥራት ለሚፈልጉ ምሩቃን በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ገብተው ተጨማሪ የመምህርነት ሙያ፣ የሚያስተምሩት ትምህርት አይነት ይዘት ፣ የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የጋራ ኮርሶችን ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋልም ተብሏል።
የመምህራንና የትምህር አመራር ልማት ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ አሰገድ ምሬሳ በበኩላቸው የሀገራችንን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል አማራጭ የስልጠና ሞዳሊቲዎች እየተጠኑ ወደ ስራ ማስገባት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም በተደረገ የዳሰሳ ጥናት አብዛኞች በተለያዩ የትምህርት መስክ የተመረቁ ተጨማሪ የማስተማር ሙያ ስልጠና ቢሰጣቸው ወደ ሙያው የመግባት ፍላጎት እንዳለም ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
የሥልጠና ማዕቀፉን ወደ ሥራ ለማስገባትም ከአሰልጣኝ የትምህርት ተቋማት፣ ከክልል ትምህርት ቢሮና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
አዲስ የተዘጋጀው አማራጭ መምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ከቀጣይ ዓመት ጀሞሮ ወደ ተግባር ይገባልም ተብሏል።
Jun 05, 2025 1.3K
Recent News
Follow Us