News

National News

ማስታወቂያ

ለፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራን አወዳድረን ለመቅጠር የምዝገባ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል።
ነገር ግን የዘንድሮ የክረምት ልዩ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች አቅም ግንባታ ስልጠና የተጠናቀቀው በቅርቡ በመሆኑ ምዝገባውን ማራዘም አስፈልጓል። በመሆኑም ምዝገባው እስከ ጳጉሜን 05/2017 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ መሆኑንን እየገለጽን ለማመልከት ፍላጎቱ ያላችሁ መምህራን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እድትመዘገቡ በድጋሚ እንገልጻለን ። ለመመዝገብ https://sbs.moe.gov.et/career/teacher ይጠቀሙ
ለፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራን አወዳድረን ለመቅጠር የምዝገባ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል።
ነገር ግን የዘንድሮ የክረምት ልዩ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች አቅም ግንባታ ስልጠና የተጠናቀቀው በቅርቡ በመሆኑ ምዝገባውን ማራዘም አስፈልጓል። በመሆኑም ምዝገባው እስከ ጳጉሜን 05/2017 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ መሆኑንን እየገለጽን ለማመልከት ፍላጎቱ ያላችሁ መምህራን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እድትመዘገቡ በድጋሚ እንገልጻለን ። ለመመዝገብ https://sbs.moe.gov.et/career/teacher ይጠቀሙ
Sep 02, 2025 944
National News

የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደገበያ የማስገባት ተግባር የሪፎርም አካል ተደርጎ በትኩረት እየተሰራበት መሆኑ ተገለጸ።

ለዩኒቨርሲቲ እንዱስትሪ ትስስር ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተሮችና የኢንኩቤሽን ማዕከላት አስተባባሪዎች ስልጠና ተሰጥቷል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ፣ የምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሃንዲሶ (ዶ/ር) በስልጠናው ላይ እንደገለጹት የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደገበያ የማስገባት ሥራ በአገር አቀፍ ደረጃ እንደዋና ዕቅድ ተይዞ እየተሰራበት ይገኛል።
በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተቋቋሙ 27 የኢንኩቤሽን ማዕከላትን የማጠናከርና ያላቋቋሙትም እንዲያቋቁሙ እየተደረገ መሆኑንም ዶ/ር ሠራዊት ተናግረዋል።
የኢንኩቤሽን ማዕከላት ማቋቋም የሥራ አጥነትን ችግር በማቃለል፣ የተግባር ልምምድ ለማድረግ በተለይም ክህሎትና ሥራ ፈጠራ ችግሮች ለመቅረፍ እንደሚያስችልም መሪ ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።
የኢንኩቤሽን ማዕከላትን ማስፋፋት በተለያዩ የትምህርት መስኮች መካከል ሊኖር የሚችለውን መስተጋብርና ቅንጅት የተሻለ በማድረግ ፈጠራና የሳይንስ ዕውቀት እንዲዳብር ለማድረግ እንደሚያግዝም ዶ/ር ሠራዊት ጨምረው አስረድተዋል።
የተቋማት ትስስር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ አቶ ተሾመ ዳንኤል በበኩለቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ ራስ ገዝነት በሚያመሩበት ወቅት በፋይናንስ ራስን የመቻል ሂደትን የሚደግፉ ተግባራትን ማከናወን ቅድምያ የሚሰጠው አማራጭ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህ እውን እንዲሆን የአዕምሯዊ ንብረትን፣ ቴክኖሎጂን እና የምርምር ውጤቶችን ወደ ገበያ በማስገብት ፤ የኢንኩቤሽን ማዕከላት ጥምረት መፍጠር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡
የሚሸጋገሩ የፈጠራ እና የቴክኖሎፐጂ ውጤቶች ተጽኖ መገምገም በሚያስችል ዲጂታል ፕላትፎረም የተደገፈ ስርዓት መዘርጋትና በፈጠራ ሀሳብ ላይ መዋለንዋያቸውን ማፍሰስ ለሚፈልጉ ኢንዱስትሪዎች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርላቸው አቶ ተሾመ አስገንዝበዋል፡፡
በትስስር አዋጅ 1298/2015 ማስፈጸሚያ መመሪያዎች፣ የምርምር እና ተክኖሎጂ ውጤቶችን ወደ ገበያ የመስገባት ሂደት እና የቢዝነስን፣ ፈጠራ እና የቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ማዕከላት አስተዳደር ዙሪያ ባተኮረው ስልጠና የዩኒቨርሲቲ እንዱስትሪ ትስስር ፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተሮችና የኢንኩቤሽን ማዕከላት አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል።
ለዩኒቨርሲቲ እንዱስትሪ ትስስር ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተሮችና የኢንኩቤሽን ማዕከላት አስተባባሪዎች ስልጠና ተሰጥቷል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ፣ የምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሃንዲሶ (ዶ/ር) በስልጠናው ላይ እንደገለጹት የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደገበያ የማስገባት ሥራ በአገር አቀፍ ደረጃ እንደዋና ዕቅድ ተይዞ እየተሰራበት ይገኛል።
በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተቋቋሙ 27 የኢንኩቤሽን ማዕከላትን የማጠናከርና ያላቋቋሙትም እንዲያቋቁሙ እየተደረገ መሆኑንም ዶ/ር ሠራዊት ተናግረዋል።
የኢንኩቤሽን ማዕከላት ማቋቋም የሥራ አጥነትን ችግር በማቃለል፣ የተግባር ልምምድ ለማድረግ በተለይም ክህሎትና ሥራ ፈጠራ ችግሮች ለመቅረፍ እንደሚያስችልም መሪ ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።
የኢንኩቤሽን ማዕከላትን ማስፋፋት በተለያዩ የትምህርት መስኮች መካከል ሊኖር የሚችለውን መስተጋብርና ቅንጅት የተሻለ በማድረግ ፈጠራና የሳይንስ ዕውቀት እንዲዳብር ለማድረግ እንደሚያግዝም ዶ/ር ሠራዊት ጨምረው አስረድተዋል።
የተቋማት ትስስር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ አቶ ተሾመ ዳንኤል በበኩለቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ ራስ ገዝነት በሚያመሩበት ወቅት በፋይናንስ ራስን የመቻል ሂደትን የሚደግፉ ተግባራትን ማከናወን ቅድምያ የሚሰጠው አማራጭ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህ እውን እንዲሆን የአዕምሯዊ ንብረትን፣ ቴክኖሎጂን እና የምርምር ውጤቶችን ወደ ገበያ በማስገብት ፤ የኢንኩቤሽን ማዕከላት ጥምረት መፍጠር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡
የሚሸጋገሩ የፈጠራ እና የቴክኖሎፐጂ ውጤቶች ተጽኖ መገምገም በሚያስችል ዲጂታል ፕላትፎረም የተደገፈ ስርዓት መዘርጋትና በፈጠራ ሀሳብ ላይ መዋለንዋያቸውን ማፍሰስ ለሚፈልጉ ኢንዱስትሪዎች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርላቸው አቶ ተሾመ አስገንዝበዋል፡፡
በትስስር አዋጅ 1298/2015 ማስፈጸሚያ መመሪያዎች፣ የምርምር እና ተክኖሎጂ ውጤቶችን ወደ ገበያ የመስገባት ሂደት እና የቢዝነስን፣ ፈጠራ እና የቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ማዕከላት አስተዳደር ዙሪያ ባተኮረው ስልጠና የዩኒቨርሲቲ እንዱስትሪ ትስስር ፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተሮችና የኢንኩቤሽን ማዕከላት አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል።
Sep 02, 2025 323
National News

ትምህርት ሚኒስቴር ከቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ልውውጥ ማዕከል ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሠነድ ተፈራረመ።

ትምህርት ሚኒስቴር ከቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ልውውጥ ማዕከል ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሠነድ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ የተቋም ለተቋም ግንኙነትን በማጠናከር የሁለቱ ሀገራት የእውቀትና ክህሎት ሽግግርን ለማሳለጥ የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ድኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ስምምነቱን በፈረሙበት ወቅት የቻይና መንግስት በኢትዬጵያ የትምህርት ልማት ዘርፍ ውስጥ ለሚያደርገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል
ሚኒስትር ድኤታው በማያያዝም ስምምነቱ ሀገራዊ ፍላጎት ላይ መሠረት በማድረግ በተለይም በማደግና በመስፋፋት ላይ ያሉ የዲጂታል፣ ሠው ሠራሽ አስተውሎ ፣ ሳይበር ሴኪዩሪቲና መሠል ትብብሮች ላይ የቻይና ባለሙያዎችንና ተቋማትን ድጋፍ እንደሚሹ አስገንዝበዋል።
መሠል ትብብሮች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በማጠናከርና ቅርርቦሽን በመፍጠር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን አጋርነትና ትብብር በበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን ሚንስትር ድኤታው በማያያዝ ገልጸዋል።
የቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ማዕከል ሀላፊ ዩ ቻንግሺዩ በበኩላቸው ቻይና አሁን ለደረሠችበት የእድገት ደረጃ የአለም አቀፍ ትብብር ያለው ሚና ወሳኝ መሆኑን ትገነዘባለች ያሉ ሲሆን በትምህርትና ተያያዥ ልውውጦች ከኢትዮጵያ ጋር ተባብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ገልጸዋል።
እንደዚህ ዓይነት ትብብሮች መጪው ትውልድ በሀገራቱ መካከል ያለውን ትብብርና ጠንካራ ወዳጅነት አብዝቶ እንዲረዳ መሠረት የሚጥል በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው የማዕከል ሀላፊው አስገንዝበዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ልውውጥ ማዕከል ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሠነድ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ የተቋም ለተቋም ግንኙነትን በማጠናከር የሁለቱ ሀገራት የእውቀትና ክህሎት ሽግግርን ለማሳለጥ የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ድኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ስምምነቱን በፈረሙበት ወቅት የቻይና መንግስት በኢትዬጵያ የትምህርት ልማት ዘርፍ ውስጥ ለሚያደርገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል
ሚኒስትር ድኤታው በማያያዝም ስምምነቱ ሀገራዊ ፍላጎት ላይ መሠረት በማድረግ በተለይም በማደግና በመስፋፋት ላይ ያሉ የዲጂታል፣ ሠው ሠራሽ አስተውሎ ፣ ሳይበር ሴኪዩሪቲና መሠል ትብብሮች ላይ የቻይና ባለሙያዎችንና ተቋማትን ድጋፍ እንደሚሹ አስገንዝበዋል።
መሠል ትብብሮች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በማጠናከርና ቅርርቦሽን በመፍጠር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን አጋርነትና ትብብር በበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን ሚንስትር ድኤታው በማያያዝ ገልጸዋል።
የቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ማዕከል ሀላፊ ዩ ቻንግሺዩ በበኩላቸው ቻይና አሁን ለደረሠችበት የእድገት ደረጃ የአለም አቀፍ ትብብር ያለው ሚና ወሳኝ መሆኑን ትገነዘባለች ያሉ ሲሆን በትምህርትና ተያያዥ ልውውጦች ከኢትዮጵያ ጋር ተባብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ገልጸዋል።
እንደዚህ ዓይነት ትብብሮች መጪው ትውልድ በሀገራቱ መካከል ያለውን ትብብርና ጠንካራ ወዳጅነት አብዝቶ እንዲረዳ መሠረት የሚጥል በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው የማዕከል ሀላፊው አስገንዝበዋል።
Aug 29, 2025 209
Advertisement

ማስታወቂያ

ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ተሰጥኦና ብቃት ያላቸው ተማሪዎች መልምሎ ልዩ ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ በፌደራል ደረጃ በተቋቋሙ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ለማስተማር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሰረት እነዚህን ትምህርት ቤቶች የሚመሩ ዳይሬክተሮችን ከመላ ሀገሪቱ አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ እና በልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ዳይሬክተር መሆን ለምትፈልጉ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አመራሮች http://sbs.moe.gov.et/directors/apply ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ተሰጥኦና ብቃት ያላቸው ተማሪዎች መልምሎ ልዩ ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ በፌደራል ደረጃ በተቋቋሙ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ለማስተማር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሰረት እነዚህን ትምህርት ቤቶች የሚመሩ ዳይሬክተሮችን ከመላ ሀገሪቱ አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ እና በልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ዳይሬክተር መሆን ለምትፈልጉ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አመራሮች http://sbs.moe.gov.et/directors/apply ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

Aug 29, 2025 566
National News

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር የተመራ የልዑካን ቡድን ተቀብለው አነጋገሩ።

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ የእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ጊላድ ሻድሞን (Gilad Shadmon) የተመራ የልዑካን ቡድን አባላትን ተቀብለው በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርቱ ዘርፍ ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትር ዴኤታው በአገራቱ መካከል የከፍተኛ ትምህርት ትብብር በተለይም በአካዳሚክ ፣ በምርምር በዩኒቨርስቲ ኢንዱስትሪ ትስስር ከእስራኤል ዩኒቨርስቲዎች ልምድና ተሞክሮ መቅሰም እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
በፈጠራና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ፣ በግብርና ፣ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፣ በማዕድንና በሌሎችም ዘርፎች ትብብር ማሳደግ እንደሚያስፈልግም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።
የእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ጊላድ ሻድመን በበኩላቸው በኢትዮጵያና በእስራኤል መካከል የቆየ ወዳጅነትና ትብብር መኖሩን ጠቁመው አገራቸው በትምህርቱ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ማጠናከር እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
እስራኤል በግብርና በአካባቢ ጥበቃ በተለይም በውሃና አፈር ጥበቃና አያያዝ፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራና በሌሎችም ያላትን ልምድ ማካፈል እንደምትችልም ገልጸዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ የእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ጊላድ ሻድሞን (Gilad Shadmon) የተመራ የልዑካን ቡድን አባላትን ተቀብለው በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርቱ ዘርፍ ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትር ዴኤታው በአገራቱ መካከል የከፍተኛ ትምህርት ትብብር በተለይም በአካዳሚክ ፣ በምርምር በዩኒቨርስቲ ኢንዱስትሪ ትስስር ከእስራኤል ዩኒቨርስቲዎች ልምድና ተሞክሮ መቅሰም እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
በፈጠራና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ፣ በግብርና ፣ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፣ በማዕድንና በሌሎችም ዘርፎች ትብብር ማሳደግ እንደሚያስፈልግም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።
የእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ጊላድ ሻድመን በበኩላቸው በኢትዮጵያና በእስራኤል መካከል የቆየ ወዳጅነትና ትብብር መኖሩን ጠቁመው አገራቸው በትምህርቱ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ማጠናከር እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
እስራኤል በግብርና በአካባቢ ጥበቃ በተለይም በውሃና አፈር ጥበቃና አያያዝ፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራና በሌሎችም ያላትን ልምድ ማካፈል እንደምትችልም ገልጸዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
Aug 29, 2025 259
National News

የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና መምህራን የሚያስተምሩትን የትምህርት ዓይነት ይዘት በአግባቡ እንዲያውቁና እንዴት ማስተማር እንደሚችሉ ግንዛቤ የተፈጠረበት እንደነበር ተጠቆመ፤ ለሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ሲሰጥ የቆየው የክረምት ልዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተጠናቋል፡፡

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) እንደገለጹት ከሐምሌ 28/2017 እስከ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ለመምህራንና የት/ቤት አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና መምህራን የሚያስተምሩትን የትምህርት ዓይነት ይዘት በአግባቡ እንዲያውቁና ለተማሪዎችም እንዴት ማስተማር እንደሚችሉ ግንዛቤ የተፈጠረበት ነበር ብለዋል፡፡
በስልጠናው መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮቹ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት ኖሯቸው ማስተማር እንዲችሉ ፣ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶችንም ተቋቁመው የመማር ማስተማር ስራን እንዴት መምራት እንዳለባቸው አቅም የገነቡበት እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
ሰልጣኝ መምህራኑ የወሰዱት የማስተማር ስነ ዘዴ ስልጠናም ወቅታዊ ችግሮችን ለመፍታትም ሆነ እየተተገበረ የሚገኘውን ስርኣተ ትምህርት በአግባቡ መተግበርና መፈጸም እንደሚያስችላቸውም ዶ/ር ሙሉቀን አብራርተዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ አሰገደች መሬሳ በበኩላቸው ከሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ከ60 እስከ 120 ሰዓት በሶስት ተከፍሎ በተሰጠው የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና 64 ሺ 900 መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን ተካፋይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በስልጠናው ከ2 ሺ 400 በላይ የሚሆኑ አሰልጣኖችም መሳተፋቸውንና 184 ሺ የስልጠና ሞጁሎች ተዘጋጅተው መሰራጨታቸውን የዴስክ ኃላፊዋ ወ/ሮ አሰገደች ተናግረዋል፡፡
ሰልጣኞቹ የድህረ ስልጠና ምዘና ፈተና በበይነ መረብ መውሰዳቸውን ጠቁመው በቀጣይ ቀናት ውስጥ የይለፍ ቃል /Password/ እና የመጠቀሚያ ስማቸውን/Username/በመጠቀም ውጤታቸውን ማየትና ከ70 በመቶ ውጤት ያመጡ ሰልጣኞችም የምስክር ወረቀታቸውንም አውርደው መውሰድ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡
በመጨረሻም ሃላፊዋ ለዚህ የመምህራንና የት/ቤት ስልጠና መሳካት አስተዋዕኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) እንደገለጹት ከሐምሌ 28/2017 እስከ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ለመምህራንና የት/ቤት አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና መምህራን የሚያስተምሩትን የትምህርት ዓይነት ይዘት በአግባቡ እንዲያውቁና ለተማሪዎችም እንዴት ማስተማር እንደሚችሉ ግንዛቤ የተፈጠረበት ነበር ብለዋል፡፡
በስልጠናው መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮቹ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት ኖሯቸው ማስተማር እንዲችሉ ፣ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶችንም ተቋቁመው የመማር ማስተማር ስራን እንዴት መምራት እንዳለባቸው አቅም የገነቡበት እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
ሰልጣኝ መምህራኑ የወሰዱት የማስተማር ስነ ዘዴ ስልጠናም ወቅታዊ ችግሮችን ለመፍታትም ሆነ እየተተገበረ የሚገኘውን ስርኣተ ትምህርት በአግባቡ መተግበርና መፈጸም እንደሚያስችላቸውም ዶ/ር ሙሉቀን አብራርተዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ አሰገደች መሬሳ በበኩላቸው ከሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ከ60 እስከ 120 ሰዓት በሶስት ተከፍሎ በተሰጠው የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና 64 ሺ 900 መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን ተካፋይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በስልጠናው ከ2 ሺ 400 በላይ የሚሆኑ አሰልጣኖችም መሳተፋቸውንና 184 ሺ የስልጠና ሞጁሎች ተዘጋጅተው መሰራጨታቸውን የዴስክ ኃላፊዋ ወ/ሮ አሰገደች ተናግረዋል፡፡
ሰልጣኞቹ የድህረ ስልጠና ምዘና ፈተና በበይነ መረብ መውሰዳቸውን ጠቁመው በቀጣይ ቀናት ውስጥ የይለፍ ቃል /Password/ እና የመጠቀሚያ ስማቸውን/Username/በመጠቀም ውጤታቸውን ማየትና ከ70 በመቶ ውጤት ያመጡ ሰልጣኞችም የምስክር ወረቀታቸውንም አውርደው መውሰድ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡
በመጨረሻም ሃላፊዋ ለዚህ የመምህራንና የት/ቤት ስልጠና መሳካት አስተዋዕኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
Aug 29, 2025 400
Advertisement

ማስታወቂያ

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ምዝገባ 

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ምዝገባ 

Aug 28, 2025 1.2K
National News

የትምህርት አገልግሎትን ከትርፍ ጋር ብቻ አያይዞ መሥራት ሀገርን እንደሚጎዳ ተገለጻ፡፡

የኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላይ አገልግሎት እየሰጡ ባሉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ባካሄደው የዳግም ምዝገባ አፈጻጸም ዙሪያ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት አገልግሎትን ከትርፍ ጋር ብቻ አያይዞ መሥራት ሀገርን እንደሚጎዳ ገልጸዋል፡፡
መንግስት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በተጠናው ጥናት መሠረት በተካሄደውና በቀጣይ በሚካሄደው ምዘና ዝቅተኛ የምዘና መስፈርቶችን የማያሟሉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከትምህርት ሥርዓቱ እንዲወጡ የሚደረግ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሀገር ሁለንተናዊ ልማት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲጫወቱ ከሀገር ወቅታዊና የወደፊት ፍላጎት እንዲሁም ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር በመቃኘት መምራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ አክለውም ይህ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የተጀመረው የብቃት ምዘና ሥራ ያለ ምንም ማዳላት በተመሳሳይ መልኩ በመንግሥት ተቋማት ላይም ተግባራዊ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው በበኩላቸው ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በዳግም ምዝገባና አስፈላጊነቱ ላይ ውይይት ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ተገቢውን መስፈርት እንዲያሟሉ ተጨማሪ ጊዜ ከተሰጣቸው ተቋማት መካከል ዕድሉን ተጠቅመው መሻሻል ያሳዩ ተቋማት እንዳሉ ገልጸዋል።
በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የተቋማት ፈቃድ አሰጣጥ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ህይወት አሰፋ ዳግም ምዝገባ ተቋማት ተዛማጅ ካልሆኑ የንግድ መስኮች ጋር ተቀላቅለው እንዳይሰሩ ፣ ህጋዊ የአሰራር ስርዓት ተከትለው እንዲሰሩ፣ በራሳቸዉ ህንጻ ወይም ሙሉ ህንጻ ተከራይተው ማስተማር እንዲችሉ፣ ሰነዶቻቸውን በአዲሱ የጥራት መስፈርት መሰረት እንዲከልሱ፣ የመምህራንን የትምህርት ዝግጅትና የቅጥር ሁኔታ በሚፈለገው ደረጃ እንዲያስተካክሉ፣ ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ማህበረሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥተዉ እንዲሰሩ የማበረታታት እና ተቋማዊ መዋቅራቸዉን በመገምገም ውጤታማ የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ፋይዳ ያለው መሆኑን አንስተዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባለቤቶችና ሃላፈዎች ተገኝተው ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን ለቀረቡት ጥያቄዎች በከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ተሰጥቷል።
የኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላይ አገልግሎት እየሰጡ ባሉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ባካሄደው የዳግም ምዝገባ አፈጻጸም ዙሪያ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት አገልግሎትን ከትርፍ ጋር ብቻ አያይዞ መሥራት ሀገርን እንደሚጎዳ ገልጸዋል፡፡
መንግስት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በተጠናው ጥናት መሠረት በተካሄደውና በቀጣይ በሚካሄደው ምዘና ዝቅተኛ የምዘና መስፈርቶችን የማያሟሉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከትምህርት ሥርዓቱ እንዲወጡ የሚደረግ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሀገር ሁለንተናዊ ልማት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲጫወቱ ከሀገር ወቅታዊና የወደፊት ፍላጎት እንዲሁም ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር በመቃኘት መምራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ አክለውም ይህ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የተጀመረው የብቃት ምዘና ሥራ ያለ ምንም ማዳላት በተመሳሳይ መልኩ በመንግሥት ተቋማት ላይም ተግባራዊ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው በበኩላቸው ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በዳግም ምዝገባና አስፈላጊነቱ ላይ ውይይት ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ተገቢውን መስፈርት እንዲያሟሉ ተጨማሪ ጊዜ ከተሰጣቸው ተቋማት መካከል ዕድሉን ተጠቅመው መሻሻል ያሳዩ ተቋማት እንዳሉ ገልጸዋል።
በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የተቋማት ፈቃድ አሰጣጥ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ህይወት አሰፋ ዳግም ምዝገባ ተቋማት ተዛማጅ ካልሆኑ የንግድ መስኮች ጋር ተቀላቅለው እንዳይሰሩ ፣ ህጋዊ የአሰራር ስርዓት ተከትለው እንዲሰሩ፣ በራሳቸዉ ህንጻ ወይም ሙሉ ህንጻ ተከራይተው ማስተማር እንዲችሉ፣ ሰነዶቻቸውን በአዲሱ የጥራት መስፈርት መሰረት እንዲከልሱ፣ የመምህራንን የትምህርት ዝግጅትና የቅጥር ሁኔታ በሚፈለገው ደረጃ እንዲያስተካክሉ፣ ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ማህበረሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥተዉ እንዲሰሩ የማበረታታት እና ተቋማዊ መዋቅራቸዉን በመገምገም ውጤታማ የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ፋይዳ ያለው መሆኑን አንስተዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባለቤቶችና ሃላፈዎች ተገኝተው ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን ለቀረቡት ጥያቄዎች በከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ተሰጥቷል።
Aug 26, 2025 649
Advertisement

ማስታዋቂያ

በ 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ እንዲደረግላችሁ የምትፈልጉ ተመሳሳይ ጾታ መንትዮች፣ የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም የተለያዩ የጤና ዕክል ያለባቸው ተማሪዎች የ 2017 ዓ.ም 12ኛ መልቀቂያ ፈተና ውጤት እስኪገለጽ ድረስ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትጠባበቁ እናሳስባለን።
የሚያስፈልጉ ሰነዶች
1. ለተመሳሳይ ጾታ መንትያ አመልካቾች
1.1. የሁለቱም አመልካቾች የልደት ካርድ
1.2. ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
2. የሚያጠቡ እናት አመልካቾች
2.1. ስድስት (6) ወር ያልሞላው የህጻኑ/ኗ የክትባት ካርድ
2.2. ከተማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
3. የተለያዩ የጤና ዕክል ያለባቸው አመልካቾች
3.1. ከመንግስት ሆስፒታሎች የቦርድ ወሳኔ የተሰጠበት የህክምና የምስክር ወረቀት
3.2. ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ የመያስፈልጉ መሆኑን እንገልጻለን።
በ 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ እንዲደረግላችሁ የምትፈልጉ ተመሳሳይ ጾታ መንትዮች፣ የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም የተለያዩ የጤና ዕክል ያለባቸው ተማሪዎች የ 2017 ዓ.ም 12ኛ መልቀቂያ ፈተና ውጤት እስኪገለጽ ድረስ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትጠባበቁ እናሳስባለን።
የሚያስፈልጉ ሰነዶች
1. ለተመሳሳይ ጾታ መንትያ አመልካቾች
1.1. የሁለቱም አመልካቾች የልደት ካርድ
1.2. ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
2. የሚያጠቡ እናት አመልካቾች
2.1. ስድስት (6) ወር ያልሞላው የህጻኑ/ኗ የክትባት ካርድ
2.2. ከተማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
3. የተለያዩ የጤና ዕክል ያለባቸው አመልካቾች
3.1. ከመንግስት ሆስፒታሎች የቦርድ ወሳኔ የተሰጠበት የህክምና የምስክር ወረቀት
3.2. ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ የመያስፈልጉ መሆኑን እንገልጻለን።
Aug 23, 2025 819
National News

እንደ ሀገር ፕሮጀክቶች ጀምሮ በፍጥነት ማጠናቀቅ በትምህርት ቤቶችም ባህል እየሆነ መምጣቱ ተገለፀ።

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ተሳታፊዎች በሲዳማ ክልል ያለውን የትምህርት እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በትምህርት ቤቶቹ ተገኝተው ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልፀው የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ገልፀዋል።
በተለይም በወንዶ ገነት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገነባው የመማሪያ ህንፃ በ8 ወር ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት እየሠጠ መሆኑን ተመልክተዋል።
ይህም እንደ ሀገር ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ የሚለው ባህል እየሆነ መምጣቱን ያሳያል ያሉ ሲሆን ሌሎች ክልሎችም ከዚህ ልምድ ሊወስዱ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የሲዳማ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ በራሳ በበኩላቸው በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የሲዳማ ተሃድሶ በሚል የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል የተሠሩ ሥራዎችን አብራርተዋል።
በተለይም እንደ ክልል ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ልዩ ትኩረት በመስጠት ተመሳሳይ ስታንዳርድ ያላቸው 78 ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በአዲስ መገንባት መቻሉን ገልፀዋል።
የጉብኝቱ ዓላማም በክልሎች መካከል ልምድ መለዋወጥ መሆኑም ተገልጿል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ተሳታፊዎች በሲዳማ ክልል ያለውን የትምህርት እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በትምህርት ቤቶቹ ተገኝተው ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልፀው የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ገልፀዋል።
በተለይም በወንዶ ገነት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገነባው የመማሪያ ህንፃ በ8 ወር ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት እየሠጠ መሆኑን ተመልክተዋል።
ይህም እንደ ሀገር ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ የሚለው ባህል እየሆነ መምጣቱን ያሳያል ያሉ ሲሆን ሌሎች ክልሎችም ከዚህ ልምድ ሊወስዱ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የሲዳማ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ በራሳ በበኩላቸው በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የሲዳማ ተሃድሶ በሚል የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል የተሠሩ ሥራዎችን አብራርተዋል።
በተለይም እንደ ክልል ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ልዩ ትኩረት በመስጠት ተመሳሳይ ስታንዳርድ ያላቸው 78 ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በአዲስ መገንባት መቻሉን ገልፀዋል።
የጉብኝቱ ዓላማም በክልሎች መካከል ልምድ መለዋወጥ መሆኑም ተገልጿል።
Aug 22, 2025 296
National News

በሀዋሳ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሀገራዊ ምክክር መድረክ የ2018 ዓ.ም የቁልፍ ተግባራት ውጤት አመላካች መለኪያዎች ላይ የጋራ ስምምነት በመፈራረም ተጠናቋል።

የትምህርት ሚኒስቴር ለሁለት ቀናት በሀዋሳ ከተማ ሲያካሄድ የነበረው የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሀገራዊ የምክክር ከሁሉም የክልልና ከተማ መስተዳድር ቢሮዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የቁልፍ ተግባራት ውጤት አመላካቾችን የስምምነት ሰነድ በመፈራረም አጠናቋል።
መድረኩ በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ በጥልቀት የተመከረበትና በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከመግባባት የተደረሰበት መሆኑ ተመላክቷል።
በመድረኩ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት ተሳትፎ፣ ጥራትና ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ ረገድ በ2017 የትምህርት ዘመን የተገኙ ስኬቶችን በማስፋትና በማስቀጠል በመጭው አመት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መድረኩ በመምከር አቅጣጫ ያስቀመጠ መሆኑን ገልፀዋል።
በዘርፉ የአፈጻጸም ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶች በመሻገር በ2018 የትምህርት ዘመን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚደረገውን ጥረትም እንዲሁ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የተመከረበት እንደሆነም ክብርት ሚንስትር ዴኤታዋ አያይዘው ገልጸዋል።
የትምህርት ለትውልድ፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የቅድመ አንደኛ ትምህርት፣ የስርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ የመምህራንና የትምህርት አመራር አቅም ግንባታ፣ ዲጂታይዜሽን እንዲሁም የወንድና ሴት ተማሪዎችን ምጥጥን አስጠብቆ የመሄድና ሌሎች መሰል የሪፎርም ስራዎች ላይ ሁሉም የክልልና ከተማ መስተዳድር ት/ቢሮዎች ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
በመጨረሻም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተዘጋጁ የተለያዩ ረቂቅ ደንቦች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ደንቦቹ ሀገራዊ ሁኔታውንና የህዝብ ፍላጎትን ያማከሉ እንዲሆኑ በቀጣይ ግብዓት የማሰባሰብ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተጠቁሟል።
የትምህርት ሚኒስቴር ለሁለት ቀናት በሀዋሳ ከተማ ሲያካሄድ የነበረው የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሀገራዊ የምክክር ከሁሉም የክልልና ከተማ መስተዳድር ቢሮዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የቁልፍ ተግባራት ውጤት አመላካቾችን የስምምነት ሰነድ በመፈራረም አጠናቋል።
መድረኩ በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ በጥልቀት የተመከረበትና በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከመግባባት የተደረሰበት መሆኑ ተመላክቷል።
በመድረኩ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት ተሳትፎ፣ ጥራትና ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ ረገድ በ2017 የትምህርት ዘመን የተገኙ ስኬቶችን በማስፋትና በማስቀጠል በመጭው አመት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መድረኩ በመምከር አቅጣጫ ያስቀመጠ መሆኑን ገልፀዋል።
በዘርፉ የአፈጻጸም ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶች በመሻገር በ2018 የትምህርት ዘመን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚደረገውን ጥረትም እንዲሁ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የተመከረበት እንደሆነም ክብርት ሚንስትር ዴኤታዋ አያይዘው ገልጸዋል።
የትምህርት ለትውልድ፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የቅድመ አንደኛ ትምህርት፣ የስርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ የመምህራንና የትምህርት አመራር አቅም ግንባታ፣ ዲጂታይዜሽን እንዲሁም የወንድና ሴት ተማሪዎችን ምጥጥን አስጠብቆ የመሄድና ሌሎች መሰል የሪፎርም ስራዎች ላይ ሁሉም የክልልና ከተማ መስተዳድር ት/ቢሮዎች ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
በመጨረሻም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተዘጋጁ የተለያዩ ረቂቅ ደንቦች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ደንቦቹ ሀገራዊ ሁኔታውንና የህዝብ ፍላጎትን ያማከሉ እንዲሆኑ በቀጣይ ግብዓት የማሰባሰብ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተጠቁሟል።
Aug 22, 2025 336
National News

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በውጭ ሀገር ካሉ አቻ ተቋማት ጋር የሚያደርጓቸውን ስምምነቶች አፈጻጸም አጠናክረው እንዲቀጥሉ ተጠየቀ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ አስተባባሪነት ኢንሃ ከተሰኘ የኮሪያ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

በስምምነት ፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትብብር ስምምነቱ በአቬሽን ሳይንስ፣ ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ እና ስማርት ሲቲ ትምህርት ፕሮግራሞችን በማጠናከር እንደሆነም ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን የአቬሽን ሳይንስ እና ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ ትምህርት ፕሮግራሞችን ለማጠናከር ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረመ ሲሆን ኢንሃ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ፕሮፌሰር ሂቸንግ ኮህ እና ጅማ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ደግሞ አቶ ኤፍሬም ዋቅጅራ ተፈራርመዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን የስማርት ሲቲ ትምህርት ፕሮግራምን ለማጠናከር ከአዲሰ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረመ ሲሆን አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲን በመወከል የዩኒቨርስቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ከማል ኢብራሂም ተፈራርመዋል፡፡
የመግባቢያ ሰነዶቹ የሚያተኩሩባቸው ቁልፍ ጉዳዮች የአቅም ግንባታ ሥልጠና፣ ምርምር እና የተማሪዎችና መምህራን ልውውጥ ከትብብር ማዕቀፎቹ መካከል ዋና ዋናዎቹ እንደሚሆኑም ተገልጿል።
የማፈራረም ሂደቱን የመሩት በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ የትብብር ማዕቀፎቹ በሶስቱም የትምህርት ፕሮግራሞች ሀገራችን ብቁ ባለሙያዎችን እንድታፈራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸውን ጠቁመው ተቋማቱ በስምምነቱ መሰረት ለውጥ ለማምጣት ጠንክረው መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ሶስቱም ተቋማት ተቋሞቻቸውን በመወከል የወሰዱትን የጋራ ሀላፊነትና አደራ በሚገባ እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
በስምምነት ፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትብብር ስምምነቱ በአቬሽን ሳይንስ፣ ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ እና ስማርት ሲቲ ትምህርት ፕሮግራሞችን በማጠናከር እንደሆነም ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን የአቬሽን ሳይንስ እና ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ ትምህርት ፕሮግራሞችን ለማጠናከር ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረመ ሲሆን ኢንሃ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ፕሮፌሰር ሂቸንግ ኮህ እና ጅማ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ደግሞ አቶ ኤፍሬም ዋቅጅራ ተፈራርመዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን የስማርት ሲቲ ትምህርት ፕሮግራምን ለማጠናከር ከአዲሰ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረመ ሲሆን አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲን በመወከል የዩኒቨርስቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ከማል ኢብራሂም ተፈራርመዋል፡፡
የመግባቢያ ሰነዶቹ የሚያተኩሩባቸው ቁልፍ ጉዳዮች የአቅም ግንባታ ሥልጠና፣ ምርምር እና የተማሪዎችና መምህራን ልውውጥ ከትብብር ማዕቀፎቹ መካከል ዋና ዋናዎቹ እንደሚሆኑም ተገልጿል።
የማፈራረም ሂደቱን የመሩት በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ የትብብር ማዕቀፎቹ በሶስቱም የትምህርት ፕሮግራሞች ሀገራችን ብቁ ባለሙያዎችን እንድታፈራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸውን ጠቁመው ተቋማቱ በስምምነቱ መሰረት ለውጥ ለማምጣት ጠንክረው መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ሶስቱም ተቋማት ተቋሞቻቸውን በመወከል የወሰዱትን የጋራ ሀላፊነትና አደራ በሚገባ እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
Aug 22, 2025 343
National News

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሀገር አቀፍ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

የዘርፉ መሪ ተዋንያኖችን ያሰባሰበው የምክክር መድረክ የ2017 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም የሚገመገምበትና የ2018 ዓ.ም እቅድ ላይ በመምከር የለውጥ ስራዎችን በላቀ ትጋት ለማስቀጠል ስምምነት የሚፈጸምበት መሆኑ ተመላክቷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት ትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርትን ለዜጎች ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለማድረስ የሚደረገውን ጥረት አጠናክሮ በማስቀጠል ረገድ ያሉ ጅምር ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ አስገነዝበዋል።
ሚንስትሩ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በመንግስት ብቻ በሚደረጉ ድጋፍና ጥረቶች የሚፈለገውን ውጤት ማስመዝገብ የማይቻል በመሆኑ በማህበረሰቡንና በሌሎች ባለድርሻ አካላት በትምህርት ለትውልድ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር እንዳለባቸው አሰገንዝበው በዚህ ረገድ የክልልና ከተማ አስተዳድር ትምህርት ቢሮዎች በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው መንግሥት ለሁሉም ዜጐች የምትመች፣ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት፣ የልማትና የብልጽግና ተስፋ የሚታይባት ኢትዮጵያን ለመገንባት የተለያዩ የለውጥ መርሃ ግብሮችን በመንደፍ በርካታ ሥራዎች እያከናወኑ መሆናቸውን ያብራሩ ሲሆን ከእነዚህ የለውጥ መርሃ ግብሮች አንዱ የትምህርት ዘርፉ የለውጥ መርሃ ግብር መሆኑን ገልጸው በዚህም በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።
ክብርት ሚንስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር አያይዘው የአምስት አመት የልማት መርሃ ግብር እንዲሁም የስድስተኛውን የትምህርት ልማት መርሃ ግብር የሚጠናቀቅበት ወቅት በመሆኑ የ2018 ዓ.ም እቅዶቻችንን ስኬታማ ለማድረግ መንደርደሪያ መሆኑን አብራርተዋል
ክቡር አቶ በየነ በራሶ የሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በክልሉ ውስጥ በመንግስትና በማህበረሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ ዋና ዋና የትምህርት ልማት ስራዎችን አብራርተዋል።
መድረኩ የተገኙ ስኬቶች ይበልጥ ለማዳበር ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በልምድ ልውውጥና ሌሎች ስልቶችን በመንደፍ ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑም ጭምር ተገልጿል።
የዘርፉ መሪ ተዋንያኖችን ያሰባሰበው የምክክር መድረክ የ2017 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም የሚገመገምበትና የ2018 ዓ.ም እቅድ ላይ በመምከር የለውጥ ስራዎችን በላቀ ትጋት ለማስቀጠል ስምምነት የሚፈጸምበት መሆኑ ተመላክቷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት ትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርትን ለዜጎች ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለማድረስ የሚደረገውን ጥረት አጠናክሮ በማስቀጠል ረገድ ያሉ ጅምር ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ አስገነዝበዋል።
ሚንስትሩ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በመንግስት ብቻ በሚደረጉ ድጋፍና ጥረቶች የሚፈለገውን ውጤት ማስመዝገብ የማይቻል በመሆኑ በማህበረሰቡንና በሌሎች ባለድርሻ አካላት በትምህርት ለትውልድ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር እንዳለባቸው አሰገንዝበው በዚህ ረገድ የክልልና ከተማ አስተዳድር ትምህርት ቢሮዎች በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው መንግሥት ለሁሉም ዜጐች የምትመች፣ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት፣ የልማትና የብልጽግና ተስፋ የሚታይባት ኢትዮጵያን ለመገንባት የተለያዩ የለውጥ መርሃ ግብሮችን በመንደፍ በርካታ ሥራዎች እያከናወኑ መሆናቸውን ያብራሩ ሲሆን ከእነዚህ የለውጥ መርሃ ግብሮች አንዱ የትምህርት ዘርፉ የለውጥ መርሃ ግብር መሆኑን ገልጸው በዚህም በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።
ክብርት ሚንስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር አያይዘው የአምስት አመት የልማት መርሃ ግብር እንዲሁም የስድስተኛውን የትምህርት ልማት መርሃ ግብር የሚጠናቀቅበት ወቅት በመሆኑ የ2018 ዓ.ም እቅዶቻችንን ስኬታማ ለማድረግ መንደርደሪያ መሆኑን አብራርተዋል
ክቡር አቶ በየነ በራሶ የሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በክልሉ ውስጥ በመንግስትና በማህበረሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ ዋና ዋና የትምህርት ልማት ስራዎችን አብራርተዋል።
መድረኩ የተገኙ ስኬቶች ይበልጥ ለማዳበር ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በልምድ ልውውጥና ሌሎች ስልቶችን በመንደፍ ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑም ጭምር ተገልጿል።
Aug 21, 2025 338
Advertisement

ማስታወቂያ

ትምህርት ሚኒስቴር ያስገነባቸውን ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን ስራ ለማስጀመር መምህራንን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል።
በመሆኑም ከስር የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟሉ መምህራን ከነሐሴ 07/2017 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት በ https://sbs.moe.gov.et/profile/teacher ላይ በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርት ሚኒስቴር ያስገነባቸውን ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን ስራ ለማስጀመር መምህራንን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል።
በመሆኑም ከስር የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟሉ መምህራን ከነሐሴ 07/2017 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት በ https://sbs.moe.gov.et/carrier/teacher ላይ በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
Aug 13, 2025 3.7K
Recent News
Follow Us