News

National News

የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል እንደሚገባ ተጠቆመ።

በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ማሰባሰብ መቻሉም ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት መጨረሻ ላይ የተጀመረውን የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ጠቁመዋል።
ትምህርት የሁሉም መሠረት እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትር ደኤታዋ በትምህርት ስርዓቱ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚሆን መሠረት ለመጣል ጠንክሮ መሥራት ይገባል ብለዋል።
በዚህም የትምህርት ስብራቱን ለማከም የሚያስችል አሻራ መጣልና ለውጥ ማምጣት እንደሚያስፈልግም ገልፀው አሁን በትምህርት ዘርፉ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተጀመሩ ሥራዎችን የበለጠ ለማላቅ በበለጠ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት አመራሮቹ እንዲሰሩም አሳስበዋል።
በትምህርት ለትውልድ መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አሰተዳደሮች ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ማሰባሰብ መቻሉም ተገለጿል።
በትምህርት ዘርፉ የተካሄደው የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ህብረተሰቡ በትምህርት ላይ ያለውን የባለቤትነት ሚና በትክክል ያረጋገጠና ለሌሎች ሴክተሮችም ተሞክሮ መሆን እንደሚችል በመድረኩ ተነስቷል።
የትምህርት ሚኒስቴር ሱፐርቪዥን ቡድን በክልሎች ያደረገው ምልከታ ሪፖርትም በመድረኩ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የሱፐርቪዥኑ ዓላማ መደጋገፍ የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በሱፐርቪዥኑ የታዩ መልካም አፈፃፀሞችን ማጠናከር እንዲሁም የታዩ ክፍተቶችን ደግሞ በቀጣይ በዕቅድ አካቶ ለመስራት እድል የሚፈጥር ነውም ተብሏል።
በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ማሰባሰብ መቻሉም ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት መጨረሻ ላይ የተጀመረውን የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ጠቁመዋል።
ትምህርት የሁሉም መሠረት እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትር ደኤታዋ በትምህርት ስርዓቱ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚሆን መሠረት ለመጣል ጠንክሮ መሥራት ይገባል ብለዋል።
በዚህም የትምህርት ስብራቱን ለማከም የሚያስችል አሻራ መጣልና ለውጥ ማምጣት እንደሚያስፈልግም ገልፀው አሁን በትምህርት ዘርፉ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተጀመሩ ሥራዎችን የበለጠ ለማላቅ በበለጠ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት አመራሮቹ እንዲሰሩም አሳስበዋል።
በትምህርት ለትውልድ መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አሰተዳደሮች ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ማሰባሰብ መቻሉም ተገለጿል።
በትምህርት ዘርፉ የተካሄደው የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ህብረተሰቡ በትምህርት ላይ ያለውን የባለቤትነት ሚና በትክክል ያረጋገጠና ለሌሎች ሴክተሮችም ተሞክሮ መሆን እንደሚችል በመድረኩ ተነስቷል።
የትምህርት ሚኒስቴር ሱፐርቪዥን ቡድን በክልሎች ያደረገው ምልከታ ሪፖርትም በመድረኩ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የሱፐርቪዥኑ ዓላማ መደጋገፍ የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በሱፐርቪዥኑ የታዩ መልካም አፈፃፀሞችን ማጠናከር እንዲሁም የታዩ ክፍተቶችን ደግሞ በቀጣይ በዕቅድ አካቶ ለመስራት እድል የሚፈጥር ነውም ተብሏል።
Apr 29, 2024 83
National News

በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ከ50 ሺ በላይ መምህራንና የትምህርት አመራሮች በክረምት ስልጠና እንደሚሠጣቸው ተገለፀ።

በዚህ ዓመት በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የመምህራን የክረምት ስልጠና ከ50 ሺ በላይ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና ይሠጣል ተብሏል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ይህ የሚሠጠው የክረምት ስልጠና አሁን እያስተማሩ ያሉ መምህራን በሚያስተምሩት የትምህርት ይዘትና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ላይ ክህሎት እንዲይዙ ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም መምህራን በሚያገኙት ስልጠና በሚያስተምሩት ትምህርት ላይ ትምህርቱን በበቂ ማስተማር የሚያስችላቸው ክህሎት ያገኛሉም ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ይህ የመምህራንና ትምህርት አመራሮች የክረምት ስልጠና የተሳካ እንዲሆን ክልሎች ተባብረው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የመምህራን የክረምት ስልጠና አተገባበር ስትራቴጂ በመምህራንና ትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱም የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ለመምህራን የሚሰጠው ስልጠና መምህራኑ በሚያስተምሩት ትምህርት ይዘትና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ላይ በመሆኑ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ጠቃሚ መሆኑንም አንስተዋል
በዚህ ዓመት በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የመምህራን የክረምት ስልጠና ከ50 ሺ በላይ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና ይሠጣል ተብሏል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ይህ የሚሠጠው የክረምት ስልጠና አሁን እያስተማሩ ያሉ መምህራን በሚያስተምሩት የትምህርት ይዘትና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ላይ ክህሎት እንዲይዙ ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም መምህራን በሚያገኙት ስልጠና በሚያስተምሩት ትምህርት ላይ ትምህርቱን በበቂ ማስተማር የሚያስችላቸው ክህሎት ያገኛሉም ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ይህ የመምህራንና ትምህርት አመራሮች የክረምት ስልጠና የተሳካ እንዲሆን ክልሎች ተባብረው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የመምህራን የክረምት ስልጠና አተገባበር ስትራቴጂ በመምህራንና ትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱም የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ለመምህራን የሚሰጠው ስልጠና መምህራኑ በሚያስተምሩት ትምህርት ይዘትና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ላይ በመሆኑ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ጠቃሚ መሆኑንም አንስተዋል
Apr 29, 2024 108
National News

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል ።
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን ለመስጠት ባይቻልም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን ይወስዳሉም ብለዋል።
የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ዶ/ር) እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናውን በኦን ላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚለቀቅላቸው ሲሆን ደጋግመው እንዲሞክሩና እንዲለማመዱ ይደረጋልም ብለዋል።
ለዚህም እንዲረዳ የአሰልጣኛች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸውም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እንደሚጀምርም በመድረኩ ተገልጿል።

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል ።
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን ለመስጠት ባይቻልም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን ይወስዳሉም ብለዋል።
የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ዶ/ር) እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናውን በኦን ላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚለቀቅላቸው ሲሆን ደጋግመው እንዲሞክሩና እንዲለማመዱ ይደረጋልም ብለዋል።
ለዚህም እንዲረዳ የአሰልጣኛች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸውም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እንደሚጀምርም በመድረኩ ተገልጿል።
Apr 27, 2024 132
National News

በትምህርት ዘርፉ ውጤታማ ስራ ለመሥራት የተግባባ፣ የጋራ አስተሳሰብ ያለውና የወደፊቱን የተገናዘበ አመራር መስጠት እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለፁ።

የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የምክክር መድረክ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልል የትምህርት ዘርፉ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
በምክክር መድረኩ የተገኙት ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የሀገራችንን የትምህርት ሥርዓት የመምራት እድል እንደተሰጠው አመራር በትምህርት ዘርፉ ውስጥ ያለውን ውስብስብ ችግር በመረዳት የተቀራረበ አመለካከት በመያዝ አመራር መስጠት ይገባል ብለዋል።
ከዚህ በፊት ትምህርትን እያየን ባለንበት መንገድ መሥራት አንችልም ያሉት ሚኒሰትሩ በረጅም ጊዜ አቅደን ብቁ ተወዳዳሪ እና በስነ-ምግባር የታነፁ ልጆች ለማፍራት የሚያስችል ትምህርት እየሰጠን ነው የሚለውን ማሰብና መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በትምህርት ዘርፍ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ የጋራ አስተሳሰብ በአዲስ መልክና ማዕቀፍ መያዝ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ከአጭር ጊዜ አስተሳሰብ ወጥተን የሚቀጥለውን ትውልድ በዓለም ተወዳዳሪ፣ ክህሎት ያለው፣ ግብረ ገብነትን የተላበሰ እንዲሆን ለማድረግ የጋራ አስተሳሰብ ይዞ መሄድ እንደሚገባም አሳስበዋል።
አሁን ዓለም ያለችበትን ሁኔታ በመረዳት የተሻለ ብቃትና ክህሎት ያላቸው እንዲሁም በስነ ምግባር የታነፁ ተማሪዎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል።
በመድረኩም የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴን ጨምሮ፣ የህዝብ ተወካዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች፣ የሁሉም ክልልና ሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የምክክር መድረክ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልል የትምህርት ዘርፉ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
በምክክር መድረኩ የተገኙት ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የሀገራችንን የትምህርት ሥርዓት የመምራት እድል እንደተሰጠው አመራር በትምህርት ዘርፉ ውስጥ ያለውን ውስብስብ ችግር በመረዳት የተቀራረበ አመለካከት በመያዝ አመራር መስጠት ይገባል ብለዋል።
ከዚህ በፊት ትምህርትን እያየን ባለንበት መንገድ መሥራት አንችልም ያሉት ሚኒሰትሩ በረጅም ጊዜ አቅደን ብቁ ተወዳዳሪ እና በስነ-ምግባር የታነፁ ልጆች ለማፍራት የሚያስችል ትምህርት እየሰጠን ነው የሚለውን ማሰብና መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በትምህርት ዘርፍ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ የጋራ አስተሳሰብ በአዲስ መልክና ማዕቀፍ መያዝ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ከአጭር ጊዜ አስተሳሰብ ወጥተን የሚቀጥለውን ትውልድ በዓለም ተወዳዳሪ፣ ክህሎት ያለው፣ ግብረ ገብነትን የተላበሰ እንዲሆን ለማድረግ የጋራ አስተሳሰብ ይዞ መሄድ እንደሚገባም አሳስበዋል።
አሁን ዓለም ያለችበትን ሁኔታ በመረዳት የተሻለ ብቃትና ክህሎት ያላቸው እንዲሁም በስነ ምግባር የታነፁ ተማሪዎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል።
በመድረኩም የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴን ጨምሮ፣ የህዝብ ተወካዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች፣ የሁሉም ክልልና ሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
Apr 26, 2024 56
National News

ሁሉም ባለድርሻና አጋር አካላት ለጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም ስኬታማነት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተጠየቀ፡፡

በኦሮሚያ ብ/ክ/መ/በአርሲ ዞን የሌሙና ብልብሎ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጫላ አበራ የቢልቢሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የጎልማሶች መማሪያ ማዕከልን ባስጎበኙበት ወቅት የህዝባችንን እኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም ሆነ የሀገራችንን እድገት ለማፋጠን ሁሉም ባለድርሻና አጋር አካላት ለጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም ስኬታማነት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባቸው ጠይቀዋል፡፡
አቶ ጫላ ለፕሮግራሙ ስኬታማነት የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት መማር የሚጠበቅባቸውን ጎልማሶች ለይቶ በማወቅ አሳምኖ ወደ ስልጠና ማዕከሉ በማምጣትም ሆነ በመማር ማስተማር ሂደቱም ላይ ቀጣይነት ያለው ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አቶ ጫላ አክለውም በያዝነው በ2016 ዓ.ም በወረዳው 4,623 ጎልማሶች በ60 የማስተማሪያ ማዕከላት ውስጥ በመማር ላይ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡
የብልብሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ጥበቡ አንበሴ ለጎልማሶች መማሪያ ማዕከሉ ከመደበኛው ትምህርት እኩል ትኩረት ሰጥተው እያስተዳደሩ መሆኑን ጠቁመው ይህ መሆኑ ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋጽኦ እንደነበረው ገልጸዋል፡፡
የማዕከሉ አመቻች መምህርት ስኳሬ ድሪባ ለፕሮግራሙ በተዘጋጀው መመሪያ መሰረት የአንድ አመት ትምህርታቸውን በውጤታማነት ያጠናቀቁ ጎልማሶች በመደበኛው ትምህርት 3ኛ ክፍል ገብተው ትምህርታቸውን መቀጠል የሚችሉ መሆኑን ጠቁመው ይህንን መብታቸውን ለመጠቀም ጥቂት የማይባሉ ጎልማሶች ከወዲሁ ከአፋን ኦሮሞ በተጨማሪ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መሰረታዊ ትምህርትም እንዲሰጣቸው መጠየቅ መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡
በኦሮሚያ ብ/ክ/መ/በአርሲ ዞን የሌሙና ብልብሎ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጫላ አበራ የቢልቢሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የጎልማሶች መማሪያ ማዕከልን ባስጎበኙበት ወቅት የህዝባችንን እኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም ሆነ የሀገራችንን እድገት ለማፋጠን ሁሉም ባለድርሻና አጋር አካላት ለጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም ስኬታማነት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባቸው ጠይቀዋል፡፡
አቶ ጫላ ለፕሮግራሙ ስኬታማነት የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት መማር የሚጠበቅባቸውን ጎልማሶች ለይቶ በማወቅ አሳምኖ ወደ ስልጠና ማዕከሉ በማምጣትም ሆነ በመማር ማስተማር ሂደቱም ላይ ቀጣይነት ያለው ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አቶ ጫላ አክለውም በያዝነው በ2016 ዓ.ም በወረዳው 4,623 ጎልማሶች በ60 የማስተማሪያ ማዕከላት ውስጥ በመማር ላይ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡
የብልብሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ጥበቡ አንበሴ ለጎልማሶች መማሪያ ማዕከሉ ከመደበኛው ትምህርት እኩል ትኩረት ሰጥተው እያስተዳደሩ መሆኑን ጠቁመው ይህ መሆኑ ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋጽኦ እንደነበረው ገልጸዋል፡፡
የማዕከሉ አመቻች መምህርት ስኳሬ ድሪባ ለፕሮግራሙ በተዘጋጀው መመሪያ መሰረት የአንድ አመት ትምህርታቸውን በውጤታማነት ያጠናቀቁ ጎልማሶች በመደበኛው ትምህርት 3ኛ ክፍል ገብተው ትምህርታቸውን መቀጠል የሚችሉ መሆኑን ጠቁመው ይህንን መብታቸውን ለመጠቀም ጥቂት የማይባሉ ጎልማሶች ከወዲሁ ከአፋን ኦሮሞ በተጨማሪ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መሰረታዊ ትምህርትም እንዲሰጣቸው መጠየቅ መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡
Apr 16, 2024 247
National News

መሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በመደበኛ ት/ቤቶች የትምህርት መጠነ-ማቋረጥን እንዲቀንስ ማድረጉ ተገለጸ

ሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ትምህርት ቢሮ የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆኑ ትምህርቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተሻለ ሸለመ እንደገለጹት በክልሉ ተግባራዊ የተደረገው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጠን መቋረጥ ፣ ማርፈድና ከትምህርት ገበታ መቅረት እንዲቀንስ አስችሏል፡፡
እንደ ሃላፊው ገለጻ በትምህርት ቤቶች መጠነ - ማቋረጥ የቀነሰው በክልሉ ሰላሳ ሰባት ወረዳዎች መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች ትምህርት የሚከታተሉ ጎልማሶችና ወላጆች የትምህርትን ጠቀሜታ በመገንዘብ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤቶች በመላካቸውና አስፈላጊውን ክትትል ማድረግ በመጀመራቸው ነው።
በክልሉ መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ማንበብ ፣ መጻፍና ማስላት የማይችሉ ጎልማሶች ማንበብና መጻፍ እንዲሁም መሰረታዊ የሂሳብ ስሎቶችን ማስላት መቻላቸውንም የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ዳይሬክተሩ አመልክተዋል።
ጎልማሶቹ ከስራቸውና ከእለት ተለት የኑሮ እንቅስቃሴዎቻቸው ጋር የተዛመዱ ትምህርቶችን በመማራቸው በቁጠባ ፣ በማዳበሪያና ምርጥ ዘር አጠቃቀም፣ በኮምፖስት ዝግጅት ፣ በዶሮ እርባታና በሌሎችም በእርሻና እንስሳት ልማት ስራዎቻቸው ውጤታማና ምርታማ መሆናቸውን አቶ ተሻለ ተናግረዋል፡፡
የዳራ ኦቲልቾ ወረዳ ትምህርት ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ ላሜሶ እና የዳራ ወረዳ ት/ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ታደሰ በበኩላቸው በወረዳው የጎልማሶች ትምህርት ማዕከላት መሰረታዊ ትምህርት የሚከታተሉ ጎልማሶች ማንበብ ፣ መጻፍና ማስላት ብቻ ሳይሆን በኑሯቸውም ለውጥ እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በክልሉ በ2016 የትምህርት ዘመን በክልሉ ሁሉም ወረዳዎች 75ሺ 443 ጎልማሶች በ 1ሺህ 320 የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች ተመዝግበው በመማር ላይ እንደሚገኙ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ትምህርት ቢሮ የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆኑ ትምህርቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተሻለ ሸለመ እንደገለጹት በክልሉ ተግባራዊ የተደረገው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጠን መቋረጥ ፣ ማርፈድና ከትምህርት ገበታ መቅረት እንዲቀንስ አስችሏል፡፡
እንደ ሃላፊው ገለጻ በትምህርት ቤቶች መጠነ - ማቋረጥ የቀነሰው በክልሉ ሰላሳ ሰባት ወረዳዎች መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች ትምህርት የሚከታተሉ ጎልማሶችና ወላጆች የትምህርትን ጠቀሜታ በመገንዘብ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤቶች በመላካቸውና አስፈላጊውን ክትትል ማድረግ በመጀመራቸው ነው።
በክልሉ መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ማንበብ ፣ መጻፍና ማስላት የማይችሉ ጎልማሶች ማንበብና መጻፍ እንዲሁም መሰረታዊ የሂሳብ ስሎቶችን ማስላት መቻላቸውንም የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ዳይሬክተሩ አመልክተዋል።
ጎልማሶቹ ከስራቸውና ከእለት ተለት የኑሮ እንቅስቃሴዎቻቸው ጋር የተዛመዱ ትምህርቶችን በመማራቸው በቁጠባ ፣ በማዳበሪያና ምርጥ ዘር አጠቃቀም፣ በኮምፖስት ዝግጅት ፣ በዶሮ እርባታና በሌሎችም በእርሻና እንስሳት ልማት ስራዎቻቸው ውጤታማና ምርታማ መሆናቸውን አቶ ተሻለ ተናግረዋል፡፡
የዳራ ኦቲልቾ ወረዳ ትምህርት ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ ላሜሶ እና የዳራ ወረዳ ት/ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ታደሰ በበኩላቸው በወረዳው የጎልማሶች ትምህርት ማዕከላት መሰረታዊ ትምህርት የሚከታተሉ ጎልማሶች ማንበብ ፣ መጻፍና ማስላት ብቻ ሳይሆን በኑሯቸውም ለውጥ እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በክልሉ በ2016 የትምህርት ዘመን በክልሉ ሁሉም ወረዳዎች 75ሺ 443 ጎልማሶች በ 1ሺህ 320 የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች ተመዝግበው በመማር ላይ እንደሚገኙ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
Apr 16, 2024 201
National News

የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም የዜጎችን የትምህርት ጥያቄ በፍጥነት እየመለሰ እንደሆነ ተገለጸ

በኦሮሚያ ብ/ክ/መንግስት በአዳማ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት መደበኛ ያልሆን ትምህርት የስራ ሂደት ባለቤት አቶ አቡ ነጋሽ በቦኩ ክ/ከተማ የዳቤ ቆጬ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የጎልማሶች መማሪያ ማዕከልን ባስጎበኙበት ወቅት የጎልማሶች መሰረታዊ ትምሀርት ፕሮግራም ውጤቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚታይ ሁለንተናዊ ፋይዳ ያለው የሰው ሀይል ልማት ስራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አቶ አቡ በአሁኑ ወቅት በአዳማ ከተማ አስተዳድር ስር 18 ማዕከላት መኖራቸውን ጠቅሰው በማዕከላቱም 21 አመቻቾችና 2,305 ጎልማሶች በመማር ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
እንደ ሃላፊው ገለጻ የከተማ መስተዳድሩ በቅርቡ ባካሄደው ሪፎርም 24 የገጠር ቀበሌዎችንና ከ40 በላይ ት/ቤቶችን ወደ ራሱ እንዳካተተ ጠቅሰው እነዚህን ሰፊ የህብረተሰብ ክፍል ለማስተማር እንዲቻል በቀጣይ የአመቻቾችን ብዛት ወደ 89 ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የትምህርት ቤቱ ሪዕሰ መምህር አቶ ያሚ ደሜ በበኩላቸው በዚህ አመት በማዕከሉ 67 ጎልማሶች በመማር ላይ ያሉ መሆኑንና ከክልል በወረደው የስራ አፈጻጸም ግምገማ መመሪያ መሰረት የጎልማሶች ማዕከል ባለባቸው ት/ቤቶች ላይ የአመራሮች የአፈጻጸም ግምገማ ይህንን ታሳቢ ያደረገ እንደሆነም ገልጸው ይሄም ለስራው ትኩረት እንዲሰጥ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ጠቁመዋል።
በማስተማር ስራ ላይ ያገኘናቸው አመቻች መምህርት ኦላንቱ መሓመድ እንደገለጹት ደግሞ ጎልማሶችን አሳምኖ ወደ ማዕከሉ ማምጣት ከባድ ቢሆንም መጥተው ፊደልና ቁጥርን መለየት ከጀመሩ በኋለ የትምህርት ፍላጎታቸውና አቀባበላቸው በዚያው ልክ እየጨመረ እንደሚሄድ ጠቅሰው ለማሳያነትም ጥቂት የማይባሉ ጎልማሶች በአመት መማር የሚጠበቅባቸውን ትምህርት በግማሽ አመቱ ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡
በማዕከሉ በመማር ላይ ያገኘናቸው ወ/ሮ ደሪቡ ህንሰርሙ ወደ ማዕከሉ ከመምጣታቸው በፊት ምንም ያልተማሩ ሲሆኑ አመቻቻቸው ቤት ለቤትና በስራ ቦታቸው ጭምር በመሄድ ባደረጉት ተደጋጋሚ የማሳመን ስራ ወደ ማዕከሉ መምጣታቸውን ጠቅሰው በአሁኑ ወቅት ማንበብ፣ መጻፍና ማስላት መቻላቸን ገልጸዋል።
በኦሮሚያ ብ/ክ/መንግስት በአዳማ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት መደበኛ ያልሆን ትምህርት የስራ ሂደት ባለቤት አቶ አቡ ነጋሽ በቦኩ ክ/ከተማ የዳቤ ቆጬ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የጎልማሶች መማሪያ ማዕከልን ባስጎበኙበት ወቅት የጎልማሶች መሰረታዊ ትምሀርት ፕሮግራም ውጤቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚታይ ሁለንተናዊ ፋይዳ ያለው የሰው ሀይል ልማት ስራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አቶ አቡ በአሁኑ ወቅት በአዳማ ከተማ አስተዳድር ስር 18 ማዕከላት መኖራቸውን ጠቅሰው በማዕከላቱም 21 አመቻቾችና 2,305 ጎልማሶች በመማር ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
እንደ ሃላፊው ገለጻ የከተማ መስተዳድሩ በቅርቡ ባካሄደው ሪፎርም 24 የገጠር ቀበሌዎችንና ከ40 በላይ ት/ቤቶችን ወደ ራሱ እንዳካተተ ጠቅሰው እነዚህን ሰፊ የህብረተሰብ ክፍል ለማስተማር እንዲቻል በቀጣይ የአመቻቾችን ብዛት ወደ 89 ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የትምህርት ቤቱ ሪዕሰ መምህር አቶ ያሚ ደሜ በበኩላቸው በዚህ አመት በማዕከሉ 67 ጎልማሶች በመማር ላይ ያሉ መሆኑንና ከክልል በወረደው የስራ አፈጻጸም ግምገማ መመሪያ መሰረት የጎልማሶች ማዕከል ባለባቸው ት/ቤቶች ላይ የአመራሮች የአፈጻጸም ግምገማ ይህንን ታሳቢ ያደረገ እንደሆነም ገልጸው ይሄም ለስራው ትኩረት እንዲሰጥ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ጠቁመዋል።
በማስተማር ስራ ላይ ያገኘናቸው አመቻች መምህርት ኦላንቱ መሓመድ እንደገለጹት ደግሞ ጎልማሶችን አሳምኖ ወደ ማዕከሉ ማምጣት ከባድ ቢሆንም መጥተው ፊደልና ቁጥርን መለየት ከጀመሩ በኋለ የትምህርት ፍላጎታቸውና አቀባበላቸው በዚያው ልክ እየጨመረ እንደሚሄድ ጠቅሰው ለማሳያነትም ጥቂት የማይባሉ ጎልማሶች በአመት መማር የሚጠበቅባቸውን ትምህርት በግማሽ አመቱ ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡
በማዕከሉ በመማር ላይ ያገኘናቸው ወ/ሮ ደሪቡ ህንሰርሙ ወደ ማዕከሉ ከመምጣታቸው በፊት ምንም ያልተማሩ ሲሆኑ አመቻቻቸው ቤት ለቤትና በስራ ቦታቸው ጭምር በመሄድ ባደረጉት ተደጋጋሚ የማሳመን ስራ ወደ ማዕከሉ መምጣታቸውን ጠቅሰው በአሁኑ ወቅት ማንበብ፣ መጻፍና ማስላት መቻላቸን ገልጸዋል።
Apr 15, 2024 173
National News

የማንበብ ፣ የመጻፍና የማስላት ክህሎትን በአንድ ዓመት ውስጥ ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው

የትምህርት ሚኒስቴር የኩባ ሊትሬሲ ሞዴልን በመጠቀም ዜጎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የማንበብ ፣ የመጻፍና የማስላት ክህሎትን እንዲያሳድጉ እያደረገ ነው። ይህንን አሰራር ወደ ሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች በማውረድ ተግባራዊ እንዲሆን እያተደረገ ሲሆን ክልሎችም በንቃት እየሰሩበት ይገኛሉ።
ከዚህ አንጻር በሲዳማ ክልል የጎልማሶችን የማንበብ፣ የመጻፍ እና የማስላት ክህሎት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቋል።
በክልሉ ከ75ሺ የሚበልጡ ጎልማሶች መሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በመከታተል ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል፡።
የሲዳማ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታፈሠ ገ/ ማርያም እንደገለጹት በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች የመማር እድል ያላገኙና ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ጎልማሶችና ወጣቶችን ወደ ትምህርት ቤት ለማምጣት እየተሰራ ነው፡፡
በክልሉ ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ጎልማሶችና ወጣቶችን ወደ ትምህርት ቤት ለማምጣትም በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የጎልማሶች ትምህርት መስጫ ጣቢያዎች እንዲከፈቱ እና ትምህርት ቤቶች የጎልማሶችን ትምህርት በኃላፊነት እንዲያስተባብሩና እንዲከታተሉ እየተደረገ መሆኑን አቶ ታፈሠ ገልጸዋል፡፡
በዚህም በክልሉ ሁሉም ወረዳዎች በ1 ሸህ 320 የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች 1 ሺህ 461 አመቻቾች በመደበኛ ቅጥር ፣ በኮንትራትና በበጎ ፈቃድ እንዲሟሉና 412 ርዕሳነ መምህራንም ተመድበው ጎልማሶችን በማስተማር ላይ መሆናቸውን ምክትል ቢሮ ኃላፊው አቶ ታፈሠ አስረድተዋል።
በአሁኑ ጊዜ በክልሉ ሰላሳ ሰባት ወረዳዎች 87 ሺ 753 ጎልማሶችን ለማስተማር ታቅዶ 75ሺ 443 ጎልማሶች ተመዝግበው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በመከታተል ላይ መሆናቸውንም ምክትል የቢሮ ኃላፊው ጨምረው ገልጸው ይሄው ፕሮግራም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የክልሉ ትምህርት ቢሮ የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተሻለ ሸለመ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ሁለት ዓመት የነበረው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ፕሮግራም እንደ ክልሉ ተጨባጭ ሁኔታ በአንድ ዓመት እንዲጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።።
መርሀ ግብሩ ቀደም ሲል የተቀናጀ ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ይባል እንደነበር ገልጸው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በመሆን ከስያሜው ጀምሮ በአሁኑ ጊዜ ለውጥ ተደርጎበት ጎልማሶችን በአንድ ዓመት የመጻፍ ፣ የማንበብ እና የማስላት ክህሎትን ማስቻል ትኩረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡።
በክልሉ የመሰረታዊ ጎልማሶች ትምህርት ከትምህርት ቤቶች በተጨማሪ በቤተ እምነቶች፣ በአርሶ አደር ማሰልጠኛ ጣቢያዎች፣ በግል ተቋማት እንዲሁም በማረሚያ ቤቶች ጭምር በመርሀ ግብሩ የሚማማሩ ጎልማሶች መኖራቸውንም ዳይሬክተሩ አቶ ተሻለ አመልክተዋል።።
የዳራ ወረዳ ትምህርት ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ታደሰ እና የዳራ አትልቾ ወረዳ ትምህርት ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ ላሚሶ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በወረዳዎቻቸው በሚገኙ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ቅጥር ግቢዎችና ከቅጥር ግቢ ውጪ በተቋቋሙ የጎልማሶች ትምህርት መስጫ ጣቢያዎች ትምህርት በመከታተል ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
በወረዳዎቹ በጎልማሶች ፍላጎትና ምርጫ በሳምንት ሁለት ቀናት ለሶስት ሰዓታት እየተሰጠ የሚገኘውን መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በሁሉም የመማማሪያ ጣቢያዎች ተጠናክሮ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር የኩባ ሊትሬሲ ሞዴልን በመጠቀም ዜጎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የማንበብ ፣ የመጻፍና የማስላት ክህሎትን እንዲያሳድጉ እያደረገ ነው። ይህንን አሰራር ወደ ሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች በማውረድ ተግባራዊ እንዲሆን እያተደረገ ሲሆን ክልሎችም በንቃት እየሰሩበት ይገኛሉ።
ከዚህ አንጻር በሲዳማ ክልል የጎልማሶችን የማንበብ፣ የመጻፍ እና የማስላት ክህሎት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቋል።
በክልሉ ከ75ሺ የሚበልጡ ጎልማሶች መሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በመከታተል ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል፡።
የሲዳማ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታፈሠ ገ/ ማርያም እንደገለጹት በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች የመማር እድል ያላገኙና ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ጎልማሶችና ወጣቶችን ወደ ትምህርት ቤት ለማምጣት እየተሰራ ነው፡፡
በክልሉ ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ጎልማሶችና ወጣቶችን ወደ ትምህርት ቤት ለማምጣትም በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የጎልማሶች ትምህርት መስጫ ጣቢያዎች እንዲከፈቱ እና ትምህርት ቤቶች የጎልማሶችን ትምህርት በኃላፊነት እንዲያስተባብሩና እንዲከታተሉ እየተደረገ መሆኑን አቶ ታፈሠ ገልጸዋል፡፡
በዚህም በክልሉ ሁሉም ወረዳዎች በ1 ሸህ 320 የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች 1 ሺህ 461 አመቻቾች በመደበኛ ቅጥር ፣ በኮንትራትና በበጎ ፈቃድ እንዲሟሉና 412 ርዕሳነ መምህራንም ተመድበው ጎልማሶችን በማስተማር ላይ መሆናቸውን ምክትል ቢሮ ኃላፊው አቶ ታፈሠ አስረድተዋል።
በአሁኑ ጊዜ በክልሉ ሰላሳ ሰባት ወረዳዎች 87 ሺ 753 ጎልማሶችን ለማስተማር ታቅዶ 75ሺ 443 ጎልማሶች ተመዝግበው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በመከታተል ላይ መሆናቸውንም ምክትል የቢሮ ኃላፊው ጨምረው ገልጸው ይሄው ፕሮግራም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የክልሉ ትምህርት ቢሮ የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተሻለ ሸለመ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ሁለት ዓመት የነበረው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ፕሮግራም እንደ ክልሉ ተጨባጭ ሁኔታ በአንድ ዓመት እንዲጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።።
መርሀ ግብሩ ቀደም ሲል የተቀናጀ ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ይባል እንደነበር ገልጸው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በመሆን ከስያሜው ጀምሮ በአሁኑ ጊዜ ለውጥ ተደርጎበት ጎልማሶችን በአንድ ዓመት የመጻፍ ፣ የማንበብ እና የማስላት ክህሎትን ማስቻል ትኩረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡።
በክልሉ የመሰረታዊ ጎልማሶች ትምህርት ከትምህርት ቤቶች በተጨማሪ በቤተ እምነቶች፣ በአርሶ አደር ማሰልጠኛ ጣቢያዎች፣ በግል ተቋማት እንዲሁም በማረሚያ ቤቶች ጭምር በመርሀ ግብሩ የሚማማሩ ጎልማሶች መኖራቸውንም ዳይሬክተሩ አቶ ተሻለ አመልክተዋል።።
የዳራ ወረዳ ትምህርት ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ታደሰ እና የዳራ አትልቾ ወረዳ ትምህርት ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ ላሚሶ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በወረዳዎቻቸው በሚገኙ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ቅጥር ግቢዎችና ከቅጥር ግቢ ውጪ በተቋቋሙ የጎልማሶች ትምህርት መስጫ ጣቢያዎች ትምህርት በመከታተል ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
በወረዳዎቹ በጎልማሶች ፍላጎትና ምርጫ በሳምንት ሁለት ቀናት ለሶስት ሰዓታት እየተሰጠ የሚገኘውን መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በሁሉም የመማማሪያ ጣቢያዎች ተጠናክሮ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
Apr 14, 2024 188
National News

የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደርን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደርን Jorge Fernando Lefebre Nicolas በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን ውይይታቸውም በኢትዮጵያና በኩባ የህክምና ትምህርት ተቋማት መካከል የተቋም ተቋም ግንኙነትን ማጠናከር፣ የምርምር ስራዎችን በጋራ መስራት፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮችና የህክምና ባለሙያዎች ልወውጥ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ነበር።
ክቡር ሚኒስትሩ ከክቡር አምባሳደሩ ጋር በነበራቸው ውይይትም የአንጋፋው የያሬድ የሙዚቃ ት/ቤትን ለማጠናከር ከአፍሮ ኪዩባን ባህላዊ ማዕከል ጋር በጋራ በሚሰሩበት ዙሪያ ስምምነት አድርገዋል። የተቋማቱ ስምምነት የሀገራቱን የባህላዊ ሙዚቃ ልውውጥ የሚያሳድግ ሲሆን ለያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ደግሞ አለምአቀፍ የሙዚቃ ባህል ልውውጥ ለማድረግ እንዲችል እድል የሚሰጥ እንደሆነ ተገልጿል።
የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደርን Jorge Fernando Lefebre Nicolas በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን ውይይታቸውም በኢትዮጵያና በኩባ የህክምና ትምህርት ተቋማት መካከል የተቋም ተቋም ግንኙነትን ማጠናከር፣ የምርምር ስራዎችን በጋራ መስራት፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮችና የህክምና ባለሙያዎች ልወውጥ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ነበር።
ክቡር ሚኒስትሩ ከክቡር አምባሳደሩ ጋር በነበራቸው ውይይትም የአንጋፋው የያሬድ የሙዚቃ ት/ቤትን ለማጠናከር ከአፍሮ ኪዩባን ባህላዊ ማዕከል ጋር በጋራ በሚሰሩበት ዙሪያ ስምምነት አድርገዋል። የተቋማቱ ስምምነት የሀገራቱን የባህላዊ ሙዚቃ ልውውጥ የሚያሳድግ ሲሆን ለያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ደግሞ አለምአቀፍ የሙዚቃ ባህል ልውውጥ ለማድረግ እንዲችል እድል የሚሰጥ እንደሆነ ተገልጿል።
Apr 11, 2024 330
National News

የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደርን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የጃፓን ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርን Shibata Hironori በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ውይይት ያደረጉ ሲሆን በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት የትምህርት ዘርፍ ትብብር ዙሪያ በጋራ ለመስራት ስምምነት አድርገዋል።
ክቡር አምባሳደር Shibata Hironori ሀገራቸው አንጋፋውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለማገዝና ከጃፓን ዩኒቨርስቲዎች ጋር ለማስተሳሰር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ክቡር አምባሳደሩ አክለውም ዩኒቨርስቲው ኦቶኖመስ ለመሆን የሚያደርገውን ሂደት ለመደገፍና ከዩኒቨርስቲው ጋር በምርምር ስራዎች ዙሪያ በጋራ ለመስራት፣ ፕሮፌሰሮች የሚያደርጉትን የልምድ ልውውጥ ለመደገፍ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
በተጨማሪም በሁለቱ ወገኖች ውይይት የጃፓን አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (JICA) አራት (4) የሚሆኑ የአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶችን በአዲሲቷ ኢትዮጵያ የት/ቤቶች ዲዛይን መሰረት ገንብቶ ለማስረከብ ስምምነት ተደርጓል።
እንደ ክቡር አምባሳደሩ ገለጻ ሀገራቸው የሁለቱን እህትማማች ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር ሀያ (20) የሚሆኑ በሂሳብና በሳይንስ ትምህርቶች ላይ የሚሰሩ ጃፓናውያን በጎ ፈቃደኞች እንደምትልክ ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም ለስምምነቱ ተግባራዊነት ሁለቱም ወገኖች በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸው ውይይታቸውን አጠናቀዋል።
የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የጃፓን ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርን Shibata Hironori በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ውይይት ያደረጉ ሲሆን በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት የትምህርት ዘርፍ ትብብር ዙሪያ በጋራ ለመስራት ስምምነት አድርገዋል።
ክቡር አምባሳደር Shibata Hironori ሀገራቸው አንጋፋውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለማገዝና ከጃፓን ዩኒቨርስቲዎች ጋር ለማስተሳሰር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ክቡር አምባሳደሩ አክለውም ዩኒቨርስቲው ኦቶኖመስ ለመሆን የሚያደርገውን ሂደት ለመደገፍና ከዩኒቨርስቲው ጋር በምርምር ስራዎች ዙሪያ በጋራ ለመስራት፣ ፕሮፌሰሮች የሚያደርጉትን የልምድ ልውውጥ ለመደገፍ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
በተጨማሪም በሁለቱ ወገኖች ውይይት የጃፓን አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (JICA) አራት (4) የሚሆኑ የአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶችን በአዲሲቷ ኢትዮጵያ የት/ቤቶች ዲዛይን መሰረት ገንብቶ ለማስረከብ ስምምነት ተደርጓል።
እንደ ክቡር አምባሳደሩ ገለጻ ሀገራቸው የሁለቱን እህትማማች ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር ሀያ (20) የሚሆኑ በሂሳብና በሳይንስ ትምህርቶች ላይ የሚሰሩ ጃፓናውያን በጎ ፈቃደኞች እንደምትልክ ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም ለስምምነቱ ተግባራዊነት ሁለቱም ወገኖች በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸው ውይይታቸውን አጠናቀዋል።
Apr 04, 2024 273
National News

ለዲጂታል ትምህርት (e-learning) ተደራሽነትና ጥራት የሚጠቅሙ አምስት የዲጂታል መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች ተመረቁ

ለዲጂታል ትምህርት (e-learning) ተደራሽነትና ጥራት የሚጠቅሙ አምስት የዲጂታል መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች በአዲስ አበባ፣ በባህርዳር፣ በድሬደዋ፣ በሀዋሳና በጅማ ዩኒቨርሲቲዎች ተመርቀዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ተወካይ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ የነዚህ ስቱዲዮዎች መገንባት መሰረታዊ ዓላማው ዩኒቨርስቲዎች የተሻሉ ባለሙያዎችን በመጠቀም ጥራቱን እና አግባብነቱን የጠበቀ የኤሌክትሮኒክ ኮርስ ቀረጻ ማካሄድ መሆኑንና ስቱዲዮ የተገነባላቸው ተቋማት በአቅራቢያቸው ለሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የየራሳቸውን ስቱዲዮ እስኪያቋቁሙ ድረስ አገልግሎት መስጠት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል፡፡
በዚህ የዲጂታል መርሃ- ግብር የመምህራንን የኤሌክትሮኒክስ ትምህርት አሰጣጥ አቅምን ለመገንባት እና የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ለማስተማር የታቀደ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም ለመማር ጊዜ የማይኖራቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሥራቸው ላይ ምንም ተጽዕኖ ሳይፈጠር ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዶ/ር ሰለሞን በነዚህ የመልቲ ዲጂታል እስቱዲዮ ግንባታ ሂደት ውስጥ የተሳታፉ አካላትን እስከ አሁን ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነው በቀጣይ በሚሠሩ ሥራዎችም ላይ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንድቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡
በአሜሪካ የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ዶ/ር ዩካኢ ምላምቦ (Yeukai Mlambo,Ph.D)የተመረቁት መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ረገድ ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚወስዱና በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ያላቸውን የማስተማሪያ ግብዓቶችና መሳሪያዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ዩካኢ ለውጡ ከልማዳዊ የማማር ማስማር ሂደት ወደ ድንበር፣ቦታና ጊዜ የማይገድበው ዲጂታል አለም የተደረገ መሠረታዊ ለውጥ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
ለዲጂታል ስቱዲዮው ከፍተኛ አስተዋጾ ካደረጉት አጋሮች መካከልም የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ያለው የዚህ ዲጂታል ስቱዲዮ መገንባት የወደፊቱን የተማሪዎችንና የወጣቶቻችንን ሥራ ፈጣሪነት በማጎለበትና ሥራ አጥነትን ከመቀነስ አንፃር ትልቅ ድርሻ ያለዉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የተገነቡ ስቱዲዮዎች የትምህርት ተደራሽነትና ጥራትን በማሻሻል በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ሀይል ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆኑን ጠቀሰው ስቱዲዮዎቹም እንዲገነቡ ለበረከቱት አስተዋጽኦ ትምህርት ሚኒስቴርን፣የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲንና የማስተር ካርድ ፋውንዴሽንን አመስግነዋል።
የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ እስቲዲዮ የተገነባላቸው የአራቱ ዩኒቨርሲቲዎች አመራር ከተገነቡ ስቱዲዮዎች በበይነመረብ ለታዳሚዎች መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተገነባው ስቱዲዮም ተጎብኝቷል፡፡
ለዲጂታል ትምህርት (e-learning) ተደራሽነትና ጥራት የሚጠቅሙ አምስት የዲጂታል መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች በአዲስ አበባ፣ በባህርዳር፣ በድሬደዋ፣ በሀዋሳና በጅማ ዩኒቨርሲቲዎች ተመርቀዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ተወካይ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ የነዚህ ስቱዲዮዎች መገንባት መሰረታዊ ዓላማው ዩኒቨርስቲዎች የተሻሉ ባለሙያዎችን በመጠቀም ጥራቱን እና አግባብነቱን የጠበቀ የኤሌክትሮኒክ ኮርስ ቀረጻ ማካሄድ መሆኑንና ስቱዲዮ የተገነባላቸው ተቋማት በአቅራቢያቸው ለሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የየራሳቸውን ስቱዲዮ እስኪያቋቁሙ ድረስ አገልግሎት መስጠት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል፡፡
በዚህ የዲጂታል መርሃ- ግብር የመምህራንን የኤሌክትሮኒክስ ትምህርት አሰጣጥ አቅምን ለመገንባት እና የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ለማስተማር የታቀደ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም ለመማር ጊዜ የማይኖራቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሥራቸው ላይ ምንም ተጽዕኖ ሳይፈጠር ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዶ/ር ሰለሞን በነዚህ የመልቲ ዲጂታል እስቱዲዮ ግንባታ ሂደት ውስጥ የተሳታፉ አካላትን እስከ አሁን ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነው በቀጣይ በሚሠሩ ሥራዎችም ላይ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንድቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡
በአሜሪካ የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ዶ/ር ዩካኢ ምላምቦ (Yeukai Mlambo,Ph.D)የተመረቁት መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ረገድ ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚወስዱና በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ያላቸውን የማስተማሪያ ግብዓቶችና መሳሪያዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ዩካኢ ለውጡ ከልማዳዊ የማማር ማስማር ሂደት ወደ ድንበር፣ቦታና ጊዜ የማይገድበው ዲጂታል አለም የተደረገ መሠረታዊ ለውጥ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
ለዲጂታል ስቱዲዮው ከፍተኛ አስተዋጾ ካደረጉት አጋሮች መካከልም የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ያለው የዚህ ዲጂታል ስቱዲዮ መገንባት የወደፊቱን የተማሪዎችንና የወጣቶቻችንን ሥራ ፈጣሪነት በማጎለበትና ሥራ አጥነትን ከመቀነስ አንፃር ትልቅ ድርሻ ያለዉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የተገነቡ ስቱዲዮዎች የትምህርት ተደራሽነትና ጥራትን በማሻሻል በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ሀይል ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆኑን ጠቀሰው ስቱዲዮዎቹም እንዲገነቡ ለበረከቱት አስተዋጽኦ ትምህርት ሚኒስቴርን፣የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲንና የማስተር ካርድ ፋውንዴሽንን አመስግነዋል።
የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ እስቲዲዮ የተገነባላቸው የአራቱ ዩኒቨርሲቲዎች አመራር ከተገነቡ ስቱዲዮዎች በበይነመረብ ለታዳሚዎች መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተገነባው ስቱዲዮም ተጎብኝቷል፡፡
Mar 05, 2024 811
National News

በአፍሪካ 9ኛው በኢትዮጰያ አምስተኛው የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ተከበረ፡፡

በአፍሪካ 9ኛው በኢትዮጰያ አምስተኛው የትምህርት ቤት ምገባ ቀን " ለሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ለተሻለ ትውልድ ግንባታ!!" በሚል መሪ ቃል በሀገር ደረጃ በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ተከበረ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበዓሉ ላይ ተገኝተው የትምህርት ቤት ምገባ ወጪ ሳይሆን በመጪው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ላይ የሚደረግ አዋጭና ዘላቂ የሰብዓዊ ልማት ኢንቨስትመንት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
መርሃ-ግብሩ በአግባቡ ከተተገበረ የልጆችን አካላዊና አዕምሮኣዊ ዕድገት በማፋጠንና ጤንነታቸውን በመጠበቅ የተማሪዎችን የትምህርት ውጤታማነት እንዲሻሻል በማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የትምህርት ቤት ምገባ እንደሃገር በመንግሰት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ያለና ከ6.2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ተጠቃሚ ያደረገ ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም የመንግስት አካላት፣የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶችና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ታዳጊዎችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመገንባት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን ጥረት ለመደገፍ እያበረከቱ ላሉት አስተዋጽኦ አመስግነው በቀጣይም ድጋፋቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከዲር ጁሃር በበኩላቸው ከተማ መስተዳድሩ ለትምህርት ቤት ምገባ ከፍተኛ ትኩረት ስጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአለም ምግብ ፕሮግራም ተወካይ ሚስተር ኤልቪስ ኦድኬ ኢትዮጵያ በዚህ አመት በትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን ተጠቃሚ በማድረግ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ መሆኑዋን ጠቅሰው በቀጣይም እ.አ.አ. በ2030 ሁሉንም የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የምገባ መርሃ ግብር ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራች ያለችው ስራ ስኬታማ እንዲሆን ተቋማቸውም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ገልጽዋል፡፡
በክብረ በዓሉ ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልልና ከተማ መስተዳደር ትምህርት ቢሮ፥ የሴክተር መ/ቤቶች ተወካዮችና አመራሮች፥ ሌሎችም ባለድርሻና አጋር አካላት እንዲሁም የዴሬደዋ ከተማ መስተዳደር አመራሮች፥ የአከባቢው ማህበረስብ ተወካዮች የተሳተፋ ሲሆን ስኬታማ የትምህርት ቤት ምገባ ስራዎች ተጎብኝተዋል ።
በአፍሪካ 9ኛው በኢትዮጰያ አምስተኛው የትምህርት ቤት ምገባ ቀን " ለሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ለተሻለ ትውልድ ግንባታ!!" በሚል መሪ ቃል በሀገር ደረጃ በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ተከበረ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበዓሉ ላይ ተገኝተው የትምህርት ቤት ምገባ ወጪ ሳይሆን በመጪው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ላይ የሚደረግ አዋጭና ዘላቂ የሰብዓዊ ልማት ኢንቨስትመንት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
መርሃ-ግብሩ በአግባቡ ከተተገበረ የልጆችን አካላዊና አዕምሮኣዊ ዕድገት በማፋጠንና ጤንነታቸውን በመጠበቅ የተማሪዎችን የትምህርት ውጤታማነት እንዲሻሻል በማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የትምህርት ቤት ምገባ እንደሃገር በመንግሰት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ያለና ከ6.2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ተጠቃሚ ያደረገ ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም የመንግስት አካላት፣የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶችና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ታዳጊዎችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመገንባት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን ጥረት ለመደገፍ እያበረከቱ ላሉት አስተዋጽኦ አመስግነው በቀጣይም ድጋፋቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከዲር ጁሃር በበኩላቸው ከተማ መስተዳድሩ ለትምህርት ቤት ምገባ ከፍተኛ ትኩረት ስጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአለም ምግብ ፕሮግራም ተወካይ ሚስተር ኤልቪስ ኦድኬ ኢትዮጵያ በዚህ አመት በትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን ተጠቃሚ በማድረግ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ መሆኑዋን ጠቅሰው በቀጣይም እ.አ.አ. በ2030 ሁሉንም የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የምገባ መርሃ ግብር ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራች ያለችው ስራ ስኬታማ እንዲሆን ተቋማቸውም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ገልጽዋል፡፡
በክብረ በዓሉ ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልልና ከተማ መስተዳደር ትምህርት ቢሮ፥ የሴክተር መ/ቤቶች ተወካዮችና አመራሮች፥ ሌሎችም ባለድርሻና አጋር አካላት እንዲሁም የዴሬደዋ ከተማ መስተዳደር አመራሮች፥ የአከባቢው ማህበረስብ ተወካዮች የተሳተፋ ሲሆን ስኬታማ የትምህርት ቤት ምገባ ስራዎች ተጎብኝተዋል ።
Mar 01, 2024 409
National News

የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች 128ኛውን የአድዋ ድል በዓል በተለያዩ ሁነቶች አከበሩ፡፡

«ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል!»በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ128ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች ሰንደቅ አላማ በጋራ በመስቀልና ሊሎች መርሃግብሮች አክብረዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ህዝቦች የነጻነት ችቦ እና አርማ በመሆኑ የድሉን እሴቶችና ቱሩፋቶች በሚገባ ጠብቆ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም 128ኛው የዓድዋ ድል በዓል እንደሃገር የዓድዋ ድል መታሰቢያ የሆነው አድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ተጠናቆ በተመረቀበት የሚከበር በመሆኑ ድሉን ድርብ ያደርገዋልም ብለዋል
ሰንደቅ ዓላማ በጋራ የመስቀል መርሃ ግብሩን ተከትሎ በማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ሃላፊ አቶ ኡመር ኢማም የውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የህዝቦች አብሮ የመኖርና የመልማት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳዮች ላይ ይህ ትውልድ ከአባቶቹ ብዙ መማር እንደሚገባው አመላክተዋል፡፡
በውይይቱ የማጣቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊው አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው የአድዋ ድል ቀደምት አባቶቻችን ብሄራቸው፣ ቋንቋቸው፣ ሀይማኖታቸው፣ባህላቸውና ሌሎች ልዩነቶቻቸው ሳይገድባቸው የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት በማስከበር ያቆዩን መሆኑን አብራርተው አሁን ያለው ትውልድ ከዚህ መማር እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
«ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል!»በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ128ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች ሰንደቅ አላማ በጋራ በመስቀልና ሊሎች መርሃግብሮች አክብረዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ህዝቦች የነጻነት ችቦ እና አርማ በመሆኑ የድሉን እሴቶችና ቱሩፋቶች በሚገባ ጠብቆ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም 128ኛው የዓድዋ ድል በዓል እንደሃገር የዓድዋ ድል መታሰቢያ የሆነው አድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ተጠናቆ በተመረቀበት የሚከበር በመሆኑ ድሉን ድርብ ያደርገዋልም ብለዋል
ሰንደቅ ዓላማ በጋራ የመስቀል መርሃ ግብሩን ተከትሎ በማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ሃላፊ አቶ ኡመር ኢማም የውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የህዝቦች አብሮ የመኖርና የመልማት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳዮች ላይ ይህ ትውልድ ከአባቶቹ ብዙ መማር እንደሚገባው አመላክተዋል፡፡
በውይይቱ የማጣቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊው አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው የአድዋ ድል ቀደምት አባቶቻችን ብሄራቸው፣ ቋንቋቸው፣ ሀይማኖታቸው፣ባህላቸውና ሌሎች ልዩነቶቻቸው ሳይገድባቸው የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት በማስከበር ያቆዩን መሆኑን አብራርተው አሁን ያለው ትውልድ ከዚህ መማር እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
Feb 29, 2024 397
National News

የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን የካቲት 22/2016 ዓ.ም ይከበራል!

የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን ነገ የካቲት 22/2016 ዓ.ም ይከበራል።
የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እኤአ አቆጣጠር ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲከበር በወሰኑት መሠረት የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በየአመቱ ማርች አንድ በህብረቱ አባል ሀገራት አስተናጋጅነት እየተከበረ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡
 
በዚህ አመትም 9ኛው የአፍሪካ ትምህርት ቤት ምገባ ቀን "አካታችና የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ ላይ መዋዕለ ንዋይን በማፍሰስ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይገባል” በሚል መሪ ቃል ነገ በድሬደዋ ከተማ ይከበራል፡፡
 
በኢትዮጵያ ከ6.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ ተጠቃሚ ሲሆኑ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራምን ማጠናከር መጠነ ማቋረጥን ለመቀነስና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ድርሻ ያለው በመሆኑ የሁሉንም ዜጋ ትብብር ይሻል!
የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን ነገ የካቲት 22/2016 ዓ.ም ይከበራል።
የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እኤአ አቆጣጠር ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲከበር በወሰኑት መሠረት የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በየአመቱ ማርች አንድ በህብረቱ አባል ሀገራት አስተናጋጅነት እየተከበረ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡
 
በዚህ አመትም 9ኛው የአፍሪካ ትምህርት ቤት ምገባ ቀን "አካታችና የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ ላይ መዋዕለ ንዋይን በማፍሰስ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይገባል” በሚል መሪ ቃል ነገ በድሬደዋ ከተማ ይከበራል፡፡
 
በኢትዮጵያ ከ6.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ ተጠቃሚ ሲሆኑ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራምን ማጠናከር መጠነ ማቋረጥን ለመቀነስና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ድርሻ ያለው በመሆኑ የሁሉንም ዜጋ ትብብር ይሻል!
Feb 29, 2024 396
Recent News
Follow Us