News

National News

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተጀመሩ ሁሉ አቀፍ የሪፎርም ስራዎች በተቀናጀ የህዝብ ግንኙነት ስራ ሊደገፉ እንደሚገባ ተገለጸ፤ የዩኒቨርስቲ የህዝብ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚዎች ፎረም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ ይገኛል።

በትምህርት ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ እንደገለጹት ዩኒቨርስቲዎች የሪፎሮም ስራዎችን በህዝብ ግንኙነት ስራ በማጀብ ለማህበረሰቡ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ ማድረስ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ እውቀት የሚገበይባቸውና ሀሳብ በነጻነት የሚራመድባቸው ተቋማት መሆናቸውንም ገልጸዋል።
አክለውም በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራት ተደራሽነት፣ተገቢነት እና ፍትሃዊነት የማረጋገጥ ስራዎችን በህዝብ ግንኙነት ስራ ማጀብ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ቦጋለ ከዚሁ ጋር አያይዘው እንደገለጹት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሃላፊዎች ሙያቸውን በሚገባ አውቀው የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ አበርክቶ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸው የትምህርት ሚኒስቴርም በማንኛውም ጊዜ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ኢንጅነር ቦጋለ ገ/ማርያም በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ፎረም መረጃዎችን ለመለዋወጥ፣ ግንኙነትን ለማጠናከርና ተሞክሮዎችን ለመቀመር እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የፎረሙ ተሳታፊዎች በዩኒቨርስቲው በሚኖራቸው ቆይታ መልካም ተሞክሮዎቹን እንደሚያጋሩና ከሌሎች ዩኒቨርስቲዎችም ጠንካራ ልምዶችን እንዲቀስሙ እድል እንደሚፈጥርላቸው ጠቅሰዋል፤
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን(ዶ/ር) በበኩላቸው የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ከጊዜ ወደ ጊዜ በቴክኖሎጂ እየተራቀቀ በመምጣቱ ይህን የተረዳና ከጊዜው ጋር የሚራመድ ኮሙኒኬሽን መተግበር እንደሚገባ ገልጸዋል።
በፎረሙ ላይ ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በትምህርት ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ እንደገለጹት ዩኒቨርስቲዎች የሪፎሮም ስራዎችን በህዝብ ግንኙነት ስራ በማጀብ ለማህበረሰቡ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ ማድረስ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ እውቀት የሚገበይባቸውና ሀሳብ በነጻነት የሚራመድባቸው ተቋማት መሆናቸውንም ገልጸዋል።
አክለውም በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራት ተደራሽነት፣ተገቢነት እና ፍትሃዊነት የማረጋገጥ ስራዎችን በህዝብ ግንኙነት ስራ ማጀብ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ቦጋለ ከዚሁ ጋር አያይዘው እንደገለጹት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሃላፊዎች ሙያቸውን በሚገባ አውቀው የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ አበርክቶ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸው የትምህርት ሚኒስቴርም በማንኛውም ጊዜ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ኢንጅነር ቦጋለ ገ/ማርያም በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ፎረም መረጃዎችን ለመለዋወጥ፣ ግንኙነትን ለማጠናከርና ተሞክሮዎችን ለመቀመር እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የፎረሙ ተሳታፊዎች በዩኒቨርስቲው በሚኖራቸው ቆይታ መልካም ተሞክሮዎቹን እንደሚያጋሩና ከሌሎች ዩኒቨርስቲዎችም ጠንካራ ልምዶችን እንዲቀስሙ እድል እንደሚፈጥርላቸው ጠቅሰዋል፤
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን(ዶ/ር) በበኩላቸው የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ከጊዜ ወደ ጊዜ በቴክኖሎጂ እየተራቀቀ በመምጣቱ ይህን የተረዳና ከጊዜው ጋር የሚራመድ ኮሙኒኬሽን መተግበር እንደሚገባ ገልጸዋል።
በፎረሙ ላይ ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
Apr 05, 2025 173
National News

የአገሪቱ ሁለንተናዊ እድገት መሰረትና ደጋፊ ለሆነው የትምህርት ዘርፍ ውጤታማነት በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ፤

“ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል ርዕስ ባለፉት ሰባት ዓመታት የለውጥ ስኬቶች ዙሪያ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች ውይይት አካሂደዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ውይይቱን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ዘርፉ የአገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እድገት መሰረት በመሆኑ በቁጭትና በእልህ በመስራት የሚፈለገው ለውጥ እንዲመጣ መረባረብ ይገባል፡፡
በአገሪቱ ባለፉት ሰባት አመታት በለውጥ ጊዜ የሚጠበቁ በርካታ ተግዳሮቶች የገጠሙና አሁንም ያለተሻገርናቸው ፈተናዎች ቢኖሩም የትምህርት ዘርፉን ጨምሮ በየዘርፉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውን አስረድተዋል፡፡
የለውጡ ጊዜ ማህበራዊ ሚዲያ ቀውስ የነገሰበት ፣ በዓለማችን አዲስ ስርዓት እተወለደ ያለበትና ልዩ ልዩ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች የተዛቡበት እና አስቸጋሪ ወቅት መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
በመሆኑም ችግሮችና ፈተናዎችን በጽናት በመቋቋም በቁጭት መስራትና አገሪቱንም ከእርዳታ ጠባቂነትና ከኋላ ቀርነት ማላቀቅና የህዝቦቿን ክብርና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲን ለማስፈን እና ከአድልዎ የጸዳ መንግስታዊ ስርዓትና መዋቅር መገንባት ወሳኝ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ አስገንዝበዋል፡፡
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከርና ከጎረቤት አገራት ጋር በመሰረተ ልማት በመተሳሰር የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የምንሰጠው ትምህርት ወቅቱ ከደረሰበት የቴክኖሎጂ እድገት ጋር ሊያራምድ የሚችል መሆኑን እየፈተሹና እያረጋገጡ መሄድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በመድረኩ “ትናንንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል ርዕስ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶች ዙሪያ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
“ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል ርዕስ ባለፉት ሰባት ዓመታት የለውጥ ስኬቶች ዙሪያ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች ውይይት አካሂደዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ውይይቱን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ዘርፉ የአገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እድገት መሰረት በመሆኑ በቁጭትና በእልህ በመስራት የሚፈለገው ለውጥ እንዲመጣ መረባረብ ይገባል፡፡
በአገሪቱ ባለፉት ሰባት አመታት በለውጥ ጊዜ የሚጠበቁ በርካታ ተግዳሮቶች የገጠሙና አሁንም ያለተሻገርናቸው ፈተናዎች ቢኖሩም የትምህርት ዘርፉን ጨምሮ በየዘርፉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውን አስረድተዋል፡፡
የለውጡ ጊዜ ማህበራዊ ሚዲያ ቀውስ የነገሰበት ፣ በዓለማችን አዲስ ስርዓት እተወለደ ያለበትና ልዩ ልዩ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች የተዛቡበት እና አስቸጋሪ ወቅት መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
በመሆኑም ችግሮችና ፈተናዎችን በጽናት በመቋቋም በቁጭት መስራትና አገሪቱንም ከእርዳታ ጠባቂነትና ከኋላ ቀርነት ማላቀቅና የህዝቦቿን ክብርና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲን ለማስፈን እና ከአድልዎ የጸዳ መንግስታዊ ስርዓትና መዋቅር መገንባት ወሳኝ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ አስገንዝበዋል፡፡
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከርና ከጎረቤት አገራት ጋር በመሰረተ ልማት በመተሳሰር የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የምንሰጠው ትምህርት ወቅቱ ከደረሰበት የቴክኖሎጂ እድገት ጋር ሊያራምድ የሚችል መሆኑን እየፈተሹና እያረጋገጡ መሄድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በመድረኩ “ትናንንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል ርዕስ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶች ዙሪያ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
Apr 02, 2025 143
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሰን አርካዲዮ ሜኔሴስ ኮፕቴን በጽ/ ቤታቸው በመቀበል ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ሁለቱ አገራት በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚችሉባቸውን ጉዳዮች አንስተው ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኮሎምቢያ አምባሳደር በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በማነጋገራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አንስተውላቸዋል።
በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በሙዚቃና ባህል ልውውጥ እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች በትብብር መስራት እንደሚቻልም አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሰን አርካዲዮ ሜኔሴስ ኮፕቴ በበኩላቸው ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ መክፈቷን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍም ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ተናግረዋል።
አክለውም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ነጻ የትምህርት እድልና የባለሙያ ልውውጥ፣ በከፍተኛ ትምህርት የሰላም ግንባታ እንዲሁም በሙዚቃና ባህል ልምድ ልውውጥ በማድረግ ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉም አንስተዋል።
ሁለቱ አካላት በቀጣይ በሚኖራቸው ግንኙነቶች በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ትብብሮችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሰን አርካዲዮ ሜኔሴስ ኮፕቴን በጽ/ ቤታቸው በመቀበል ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ሁለቱ አገራት በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚችሉባቸውን ጉዳዮች አንስተው ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኮሎምቢያ አምባሳደር በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በማነጋገራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አንስተውላቸዋል።
በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በሙዚቃና ባህል ልውውጥ እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች በትብብር መስራት እንደሚቻልም አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሰን አርካዲዮ ሜኔሴስ ኮፕቴ በበኩላቸው ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ መክፈቷን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍም ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ተናግረዋል።
አክለውም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ነጻ የትምህርት እድልና የባለሙያ ልውውጥ፣ በከፍተኛ ትምህርት የሰላም ግንባታ እንዲሁም በሙዚቃና ባህል ልምድ ልውውጥ በማድረግ ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉም አንስተዋል።
ሁለቱ አካላት በቀጣይ በሚኖራቸው ግንኙነቶች በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ትብብሮችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
Apr 01, 2025 115
National News

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በ2017 ዓ.ም ሊተገበሩ በታቀዱ የቁልፍ አፈጻጸም አመላካች ተግባራት እቅድ ላይ ከዘርፉ መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር የመግባቢያ ስምምነት ውል ተፈራረሙ፤

የከፍትኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ውሉን የተፈራረሙት መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች የአስተዳደርና መሰረተ ልማት፣የአካዳሚክ ጉዳዮች፣የምርምርና ማህበተሰብ ጉድኝት እና የኣይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች ናቸው፡፡
የተፈረመው ውል ሀላፊነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ተመላክቷል።
የመግባቢያ ስምምነት ውል መፈራረሙ ውጤት የሚያስመዘግቡ ሥራ አስፋጻሚዎች የበለጠ የሚበረታቱበት፣ ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚያስመዘግቡት ደግሞ ተጠያቂ የሚሆኑበት ሥርዓትን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሆነም ተገልጿል።
የመግባቢያ ስምምነቱ ውል ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ሥርዓት እንዲኖርና ስራ አስፈጻሚዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚያደርግም ተመላክቷል።
በመሆኑም አራቱም የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች በገቡት የመግባቢያ ስምምነት ውል መሠረት ስራዎቻቸውን ወደ ስራ ክፍሎች (ዴስኮች) በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ቀጣይነት ያለው ውጤት ማስመዝገብ አንደሚጠበቅባቸው ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
ከወራት በፊት ትምህርት ሚኒስቴር ተመሳሳይ የመግባቢያ ስምምነት ውል ከ47 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መፈራረሙ የሚታወስ ሲሆን የትምህርት ሚኒስቴርን በመወከል የተፈራረሙት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ሲሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹን በመወከል የተፈራረሙት የየዩኒቨርስቲዎቹ የአስተዳደር ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚዳንቶች መሆናቸው ይታወሳል።
የከፍትኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ውሉን የተፈራረሙት መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች የአስተዳደርና መሰረተ ልማት፣የአካዳሚክ ጉዳዮች፣የምርምርና ማህበተሰብ ጉድኝት እና የኣይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች ናቸው፡፡
የተፈረመው ውል ሀላፊነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ተመላክቷል።
የመግባቢያ ስምምነት ውል መፈራረሙ ውጤት የሚያስመዘግቡ ሥራ አስፋጻሚዎች የበለጠ የሚበረታቱበት፣ ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚያስመዘግቡት ደግሞ ተጠያቂ የሚሆኑበት ሥርዓትን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሆነም ተገልጿል።
የመግባቢያ ስምምነቱ ውል ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ሥርዓት እንዲኖርና ስራ አስፈጻሚዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚያደርግም ተመላክቷል።
በመሆኑም አራቱም የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች በገቡት የመግባቢያ ስምምነት ውል መሠረት ስራዎቻቸውን ወደ ስራ ክፍሎች (ዴስኮች) በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ቀጣይነት ያለው ውጤት ማስመዝገብ አንደሚጠበቅባቸው ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
ከወራት በፊት ትምህርት ሚኒስቴር ተመሳሳይ የመግባቢያ ስምምነት ውል ከ47 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መፈራረሙ የሚታወስ ሲሆን የትምህርት ሚኒስቴርን በመወከል የተፈራረሙት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ሲሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹን በመወከል የተፈራረሙት የየዩኒቨርስቲዎቹ የአስተዳደር ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚዳንቶች መሆናቸው ይታወሳል።
Mar 31, 2025 157
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፍልሰት ዙሪያ በሳይንሳዊ ምርምሮች የተደገፉ ስራዎችን በማቅረብ ችግሩ እንዲቀረፍ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ።

ትምህርት ሚኒስቴር ዴዚም /Dezim / እና ሶሊሲቲ/ Soli*City/ ከተባሉ ሁለት ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡።
የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በስምምነቱ ወቅት እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በስደተኝነና ፍልሰት ዙሪያ ሳይንሳዊ ምርምሮችን በማድረግ ለፖሊሲ ግብኣት የሚሆኑ ሀሳቦችን ሊያመነጩ ይገባል፡።
ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒቨርስቲዎች ጋር በቅርቡ ከተፈራረማቸው KPI / ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች/ ውስጥ አንዱ ዩኒቨርስቲዎች እንደሚገኙበት ተጨባጭ ሁኔታ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ሕገ-ወጥ ፍልሰትን በመከላከል ማህበራዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደሚገኝበት ጠቁመዋል፡፡
በተለይም ችግሩ በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መንግስት ችግሩን ለመቀነስ የሚያካሂደውን የፖሊሲ እርምጃ ለመደፍና ወደፊት ለማራመድ ጥልቅ ምርምር ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል፡፡
ዴዚል እና ሶሊሲቲ ከተባሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት መሰረት የሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ ተቋማቱ የተሻለ ምርምር ለመስራት እድል እንደሚፈጥርላቸውም ክቡር ሚኒስተር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ተጠባባቂ መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው የፍልሰተኝነትና ስደተኝንነት ችግሮች በምርምር ከመፍታት አንጻር ሰፊ ክፍተት መኖሩን ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ራሳቸውን በመፈተሽ በምርምር የተደገፉ ተጽዕኖ ፈጣሪ መረጃዎችን ማመንጨት፣ ወደሌሎች ተቋማት ማስፋትና በተጠያቂነትና በኃላፊነት ችግሩን በጋራ ለመፍታት መስራት እንደሚገባቸውም ዶ/ር ሰራዊት ጨምረው ገልጸዋል፡፡፡
ሶሊሲቲን በመወከል የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት ፕሮፌሰር ሃራልድ ባውደር በበኩላቸው ትብብሩ በአፍሪካ ቀንድ በኩል የሚደረገውን ፍልሰት በመረዳት በመረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ ለማውጣትና ለችግር የተጋለጡ ስደተኖችንና ፍልሰተኖችን ለመርዳት እንደሚያስችል ተናግረዋል፡።
የጀርመን የውህደት እና የፍልሰት ጥናት ማእከል (DeZIM) ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ኖአ ኬ ሃ በበኩላቸው ስምምነቱ ተቋማቸው በፍልሰተኞችና ስደተኞች ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስቴርና ከዩኒቨርሲቲ የምርምር ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት እንደሚያስችለው ተናግረዋል፡።
በፊርማ ስምምነቱ ወቅት በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሰባት ዩኒቨርስቲ የምርምር ምክትል ፕሬዚዳንቶች ፣ የፍትህ ሚኒስቴርና ከሌሎችም የተውጣጡ ባለድርሻዎች ተገኝተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ዴዚም /Dezim / እና ሶሊሲቲ/ Soli*City/ ከተባሉ ሁለት ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡።
የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በስምምነቱ ወቅት እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በስደተኝነና ፍልሰት ዙሪያ ሳይንሳዊ ምርምሮችን በማድረግ ለፖሊሲ ግብኣት የሚሆኑ ሀሳቦችን ሊያመነጩ ይገባል፡።
ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒቨርስቲዎች ጋር በቅርቡ ከተፈራረማቸው KPI / ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች/ ውስጥ አንዱ ዩኒቨርስቲዎች እንደሚገኙበት ተጨባጭ ሁኔታ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ሕገ-ወጥ ፍልሰትን በመከላከል ማህበራዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደሚገኝበት ጠቁመዋል፡፡
በተለይም ችግሩ በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መንግስት ችግሩን ለመቀነስ የሚያካሂደውን የፖሊሲ እርምጃ ለመደፍና ወደፊት ለማራመድ ጥልቅ ምርምር ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል፡፡
ዴዚል እና ሶሊሲቲ ከተባሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት መሰረት የሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ ተቋማቱ የተሻለ ምርምር ለመስራት እድል እንደሚፈጥርላቸውም ክቡር ሚኒስተር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ተጠባባቂ መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው የፍልሰተኝነትና ስደተኝንነት ችግሮች በምርምር ከመፍታት አንጻር ሰፊ ክፍተት መኖሩን ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ራሳቸውን በመፈተሽ በምርምር የተደገፉ ተጽዕኖ ፈጣሪ መረጃዎችን ማመንጨት፣ ወደሌሎች ተቋማት ማስፋትና በተጠያቂነትና በኃላፊነት ችግሩን በጋራ ለመፍታት መስራት እንደሚገባቸውም ዶ/ር ሰራዊት ጨምረው ገልጸዋል፡፡፡
ሶሊሲቲን በመወከል የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት ፕሮፌሰር ሃራልድ ባውደር በበኩላቸው ትብብሩ በአፍሪካ ቀንድ በኩል የሚደረገውን ፍልሰት በመረዳት በመረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ ለማውጣትና ለችግር የተጋለጡ ስደተኖችንና ፍልሰተኖችን ለመርዳት እንደሚያስችል ተናግረዋል፡።
የጀርመን የውህደት እና የፍልሰት ጥናት ማእከል (DeZIM) ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ኖአ ኬ ሃ በበኩላቸው ስምምነቱ ተቋማቸው በፍልሰተኞችና ስደተኞች ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስቴርና ከዩኒቨርሲቲ የምርምር ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት እንደሚያስችለው ተናግረዋል፡።
በፊርማ ስምምነቱ ወቅት በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሰባት ዩኒቨርስቲ የምርምር ምክትል ፕሬዚዳንቶች ፣ የፍትህ ሚኒስቴርና ከሌሎችም የተውጣጡ ባለድርሻዎች ተገኝተዋል።
Mar 29, 2025 119
National News

ኢትዮጵያ እና ፊላንድ በትምህርቱ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚችሉበት ዙሪያ ተወያዩ።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የላቲን አሜሪካ ጉዳዮች ኃላፊ አምባሳደር ሄሌና አይራክሲነን ከተመራ ልዑካን ቡድን ጋር በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትምህርት ዘርፍ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ ያሉ ዋና ዋና ተግባራትን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተውለቸዋል።
በተለይም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በዚህም ማናቸውም የሚደረጉ ድጋፎች በመነጋገር ካለምንም የሀብት መባከን በትክክል ህፃናት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ እንዲውሉ ማድረግ እንደሚገባም አፅንኦት ሰጥተዋል
የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም የአካቶ ትምህርት ማዕከላትን በማስፋፋት ረገድ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
አሁንም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በምንሰራቸው የለውጥ ተግባራት የበለጠ ድጋፍ እንፈልጋለን ብለዋል።
በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የላቲን አሜሪካ ጉዳዮች ኃላፊ አምባሳደር ሄሌና አይራክሲነን በበኩላቸው በትምህርቱ ዘርፍ ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር በርካታ ተግባራትን ማከናወኗን ጠቅሰዋል።
ይህንን በማጠናከር በትምህርቱ ዘርፍ ዘርፈ ብዙ ትብብሮችን ማድረግ እንደሚፈልጉ ገልፀዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት በትምህርቱ ዘርፍ በርካታ ትብብር የሚያደርጉባቸው ጉዳዮች እንዳሉ የተወያዩ ሲሆን ማናቸውም የሚደረጉ ድጋፎች በሚኒስቴሩ በተለዩ የቅድሚያ ቅድሚያ በተሰጣቸው ጉዳዮች ላይ እንዲሆንም ተስማምተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የላቲን አሜሪካ ጉዳዮች ኃላፊ አምባሳደር ሄሌና አይራክሲነን ከተመራ ልዑካን ቡድን ጋር በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትምህርት ዘርፍ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ ያሉ ዋና ዋና ተግባራትን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተውለቸዋል።
በተለይም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በዚህም ማናቸውም የሚደረጉ ድጋፎች በመነጋገር ካለምንም የሀብት መባከን በትክክል ህፃናት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ እንዲውሉ ማድረግ እንደሚገባም አፅንኦት ሰጥተዋል
የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም የአካቶ ትምህርት ማዕከላትን በማስፋፋት ረገድ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
አሁንም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በምንሰራቸው የለውጥ ተግባራት የበለጠ ድጋፍ እንፈልጋለን ብለዋል።
በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የላቲን አሜሪካ ጉዳዮች ኃላፊ አምባሳደር ሄሌና አይራክሲነን በበኩላቸው በትምህርቱ ዘርፍ ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር በርካታ ተግባራትን ማከናወኗን ጠቅሰዋል።
ይህንን በማጠናከር በትምህርቱ ዘርፍ ዘርፈ ብዙ ትብብሮችን ማድረግ እንደሚፈልጉ ገልፀዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት በትምህርቱ ዘርፍ በርካታ ትብብር የሚያደርጉባቸው ጉዳዮች እንዳሉ የተወያዩ ሲሆን ማናቸውም የሚደረጉ ድጋፎች በሚኒስቴሩ በተለዩ የቅድሚያ ቅድሚያ በተሰጣቸው ጉዳዮች ላይ እንዲሆንም ተስማምተዋል።
Mar 22, 2025 567
National News

የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች የብቃት ማረጋገጫ ምዝገባና እውቅና ሥርዓት ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑ ተገለፀ።

የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ያጋጠማቸውን ችግሮች በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
በምክክር መድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በነበረው የትምህርት ሥርዓት ችግር መሠረታዊ የሞራል ውድቀት አጋጥሟል፤
ይህንንም ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ በአጠቃላይ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት የተለያዩ ሪፎርሞች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን አንስተዋል።
እነዚህ የተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ መምህራን ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ለዚህም የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ጥራትና ብቃት ያላቸው መምህራንን በማፍራት ረገድ ተልኳቸውን እንዲወጡ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተዋል።
በመምህራን ስልጠና ረገድ ሃገራችን ረዘም ያለ ታሪክ ያላት መሆኗን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታዋ አሁን ባለው ሁኔታ በሚያስተምሩበት የትምህርት ደረጃ በቂ ችሎታ ያላቸው መምህራንን በማፍራት ረገድ ተግዳሮቶች ገጥመዋል ብለዋል።
በዚህም ከመምህራን ስልጠና እና አስተዳደር ጋር የተያያዙ ችግሮችን በሚገባ ለይቶ መፍታት ካልተቻለ የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ እንደማይቻል ጠቅሰው ይህንን ለመፍታት ርብርብ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የጥራት ኦዲት መሪ ሥራ አስፈፃማ ወ/ሮ ትዕግስት ሃ/ስላሴ በበኩላቸው የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ሥራቸውን በሚገባ እንዲሰሩ ወደ ብቃት ማረጋገጫ ምዝገባና እውቅና ሥርዓት እንዲገቡ ማድረግ ይገባል ያሉ ሲሆን፤
በቀጣይ ኮሌጆቹ ምዝገባ በማድረግ የብቃት ማረጋገጫ እውቅና ተሰጥቷቸው የሚንቀሳቀሱበት ሥርዓት ተግባራዊ ይደረጋልም ብለዋል።
በመድረኩም ኮሌጆቹ ጥራትና ብቃት ያላቸው መምህራንን በማፍራት ረገድ ተልዕኳቸውን እንዲወጡ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆኑ ሁሉም ባለድርሻ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
በምክክር መድረኩ የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ የመምህራን ኮሌጅ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል።
የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ያጋጠማቸውን ችግሮች በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
በምክክር መድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በነበረው የትምህርት ሥርዓት ችግር መሠረታዊ የሞራል ውድቀት አጋጥሟል፤
ይህንንም ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ በአጠቃላይ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት የተለያዩ ሪፎርሞች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን አንስተዋል።
እነዚህ የተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ መምህራን ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ለዚህም የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ጥራትና ብቃት ያላቸው መምህራንን በማፍራት ረገድ ተልኳቸውን እንዲወጡ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ድርሻ የላቀ መሆኑን አንስተዋል።
በመምህራን ስልጠና ረገድ ሃገራችን ረዘም ያለ ታሪክ ያላት መሆኗን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታዋ አሁን ባለው ሁኔታ በሚያስተምሩበት የትምህርት ደረጃ በቂ ችሎታ ያላቸው መምህራንን በማፍራት ረገድ ተግዳሮቶች ገጥመዋል ብለዋል።
በዚህም ከመምህራን ስልጠና እና አስተዳደር ጋር የተያያዙ ችግሮችን በሚገባ ለይቶ መፍታት ካልተቻለ የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ እንደማይቻል ጠቅሰው ይህንን ለመፍታት ርብርብ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የጥራት ኦዲት መሪ ሥራ አስፈፃማ ወ/ሮ ትዕግስት ሃ/ስላሴ በበኩላቸው የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ሥራቸውን በሚገባ እንዲሰሩ ወደ ብቃት ማረጋገጫ ምዝገባና እውቅና ሥርዓት እንዲገቡ ማድረግ ይገባል ያሉ ሲሆን፤
በቀጣይ ኮሌጆቹ ምዝገባ በማድረግ የብቃት ማረጋገጫ እውቅና ተሰጥቷቸው የሚንቀሳቀሱበት ሥርዓት ተግባራዊ ይደረጋልም ብለዋል።
በመድረኩም ኮሌጆቹ ጥራትና ብቃት ያላቸው መምህራንን በማፍራት ረገድ ተልዕኳቸውን እንዲወጡ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆኑ ሁሉም ባለድርሻ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
በምክክር መድረኩ የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ የመምህራን ኮሌጅ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል።
Mar 18, 2025 90
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ጋር ተወያዩ፤

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ጋር በትምህርት ዘርፉ በትብብር ሊሰሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓትን ለማስተካከል የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ያሉ የሪፎርም ሥራዎችን ለአምባሳደሩ አብራርተውላቸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር እየተወሰዱ ያሉ ሪፎርሞችና የተያዙ ራዕዮችን እንገነዘባለን ያሉ ሲሆን በቀጣይ የትምህርት ዘርፉን ለመደገፍ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይቶች ለትምህርት ዘርፉ የሚደረጉ ድጋፎች ለታለመላቸው አላማ ይውሉ ዘንድ ከመተግበራቸው አስቀድሞ መወያየት እንደሚያስፈልግም ተስማምተዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ጋር በትምህርት ዘርፉ በትብብር ሊሰሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓትን ለማስተካከል የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ያሉ የሪፎርም ሥራዎችን ለአምባሳደሩ አብራርተውላቸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር እየተወሰዱ ያሉ ሪፎርሞችና የተያዙ ራዕዮችን እንገነዘባለን ያሉ ሲሆን በቀጣይ የትምህርት ዘርፉን ለመደገፍ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይቶች ለትምህርት ዘርፉ የሚደረጉ ድጋፎች ለታለመላቸው አላማ ይውሉ ዘንድ ከመተግበራቸው አስቀድሞ መወያየት እንደሚያስፈልግም ተስማምተዋል፡፡
Mar 14, 2025 87
National News

የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራም ብቃት ማዕቀፍ ለትግበራ መሆኑ ተገለጸ፤

በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተዘጋጀው የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት ብቃት ማረጋገጫ ማስፈጸሚያ ሠነድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ የተገኙት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች በትግበራ ላይ መሆናቸውን አንስተዋል።
በዚህም የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት የሥርዓተ ትምህርት ለውጥና የመውጫ ፈተና እንዲሁም በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ብሄራዊ የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑን አንስተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚጠበቅባቸውን ተልዕኮ በሚገባ እንዲወጡም በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ሚንስትር ዴኤታው ለውይይት የቀረበው የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት ብቃት ማረጋገጫ ማስፈጸሚያ ሠነድ ዝግጅትና ትግበራም የዚሁ አካል መሆኑን አስገንዝበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሜጄና በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር በአዋጅ የተሠጠውን ተልዕኮ ለማስፈጸም በርካታ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑን ያነሱ ሲሆን የተዘጋጀው የ3ኛ ዲግሪ ትምህርት ብቃት ማረጋገጫ ማስፈጸሚያ ሠነድ በየደረጃው ላሉ የስራ ሀላፊዎች፣ አሠልጣኞችና ሠልጣኞች ወጥ የሆነ አሠራር ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራምንና ስርዓተ-ትምህርትን ከማዕቀፉ ጋር በማገናዘብ እንዲተገብሩ አሳስበዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተዘጋጀው የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት ብቃት ማረጋገጫ ማስፈጸሚያ ሠነድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ የተገኙት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች በትግበራ ላይ መሆናቸውን አንስተዋል።
በዚህም የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት የሥርዓተ ትምህርት ለውጥና የመውጫ ፈተና እንዲሁም በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ብሄራዊ የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑን አንስተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚጠበቅባቸውን ተልዕኮ በሚገባ እንዲወጡም በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ሚንስትር ዴኤታው ለውይይት የቀረበው የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት ብቃት ማረጋገጫ ማስፈጸሚያ ሠነድ ዝግጅትና ትግበራም የዚሁ አካል መሆኑን አስገንዝበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሜጄና በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር በአዋጅ የተሠጠውን ተልዕኮ ለማስፈጸም በርካታ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑን ያነሱ ሲሆን የተዘጋጀው የ3ኛ ዲግሪ ትምህርት ብቃት ማረጋገጫ ማስፈጸሚያ ሠነድ በየደረጃው ላሉ የስራ ሀላፊዎች፣ አሠልጣኞችና ሠልጣኞች ወጥ የሆነ አሠራር ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራምንና ስርዓተ-ትምህርትን ከማዕቀፉ ጋር በማገናዘብ እንዲተገብሩ አሳስበዋል።
Mar 14, 2025 91
National News

የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ብቃትና ጥራት ያላቸውን መምህራን ማፍራት እንዲችሉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።

የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች የማሰልጠን አቅማቸውን ለማሳደግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
በመድረኩም የመምህራን ስልጠና ከአጀማመሩ ጀምሮ እስካሁን የሄደባቸው መንገዶችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለውይይት መነሻ ፅሁፍ ቀርቧል።
በዚሁ ጊዜ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ተዋናዩ ብዙ ቢሆንም መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ድርሻ ትልቅ መሆኑን ጠቁመው የዚህ መድረክ አላማም በመምህራን ስልጠና ያሉ ተግዳሮቶችን ነቅሶ በማውጣት የጋራ መግባባት በመፍጠር ሥራዎችን በውጤታማነት መስራት ማስቻል መሆኑም ገልጸዋል።
አክለውም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የመምህራንን አቅም ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት ዓመታት የመምህራን ስልጠና ሥርዓትን ለማሻሻል የተለያዩ ዘዴዎች ተዘርግተው ተግባራዊ ቢደረጉም ችግሩን በመሠረታዊነት ሊፈቱ አልቻሉም ያሉ ሲሆን፣
አሁን እነዚህን ተግዳሮቶች በማስተካከል ብቃትና ጥራት ያላቸው መምህራንን ለማፍራት እንዲቻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አክለውም በስራ ላይ ያሉ መምህራንን አቅም ለማሻሻልም ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተዘጋጅቶ እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰው ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።
በመድረኩም መምህራንን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል እና ሌሎች እጩ ሰልጣኞች ሙያውን ወደው እንዲመጡ የሚያስችሉ የተለያዩ የማበረታቻ ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባም ተጠቁሟል።
ተሳታፊ ባለድርሻ አካላትም የተለያዩ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች የማሰልጠን አቅማቸውን ለማሳደግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
በመድረኩም የመምህራን ስልጠና ከአጀማመሩ ጀምሮ እስካሁን የሄደባቸው መንገዶችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለውይይት መነሻ ፅሁፍ ቀርቧል።
በዚሁ ጊዜ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ተዋናዩ ብዙ ቢሆንም መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ድርሻ ትልቅ መሆኑን ጠቁመው የዚህ መድረክ አላማም በመምህራን ስልጠና ያሉ ተግዳሮቶችን ነቅሶ በማውጣት የጋራ መግባባት በመፍጠር ሥራዎችን በውጤታማነት መስራት ማስቻል መሆኑም ገልጸዋል።
አክለውም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የመምህራንን አቅም ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት ዓመታት የመምህራን ስልጠና ሥርዓትን ለማሻሻል የተለያዩ ዘዴዎች ተዘርግተው ተግባራዊ ቢደረጉም ችግሩን በመሠረታዊነት ሊፈቱ አልቻሉም ያሉ ሲሆን፣
አሁን እነዚህን ተግዳሮቶች በማስተካከል ብቃትና ጥራት ያላቸው መምህራንን ለማፍራት እንዲቻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አክለውም በስራ ላይ ያሉ መምህራንን አቅም ለማሻሻልም ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተዘጋጅቶ እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰው ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።
በመድረኩም መምህራንን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል እና ሌሎች እጩ ሰልጣኞች ሙያውን ወደው እንዲመጡ የሚያስችሉ የተለያዩ የማበረታቻ ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባም ተጠቁሟል።
ተሳታፊ ባለድርሻ አካላትም የተለያዩ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Mar 14, 2025 90
National News

የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አመራሮች የተሰጣቸውን ኃላፊነት በሚገባ እንዲወጡ ተጠየቀ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባላት የምክክር መድረክ እየተካሄድ ይገኛል፡፡

በምክክር መድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እየተወሰዱ ባሉ የሪፎርም እርምጃዎች ዩኒቨርሲቲዎች ወደፊት ምን አይነት ደረጃ ላይ መድረስ እንዳለባቸው የሚያመላክቱ በመሆኑ የሥራ አመራር ቦርድ አመራሮች ዩኒቨርሲቲዎችን ለመቀየር እየተሄደበት ያለውን ሁኔታ አውቃችሁ በዛ ልክ ኃላፊነታችሁን ልትወጡ ይገባል ብለዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አመራሮ ዩኒቨርሲቲዎች ካላቸው ራዕይና ተልዕኮ አንጻር የሰሯቸውን ሥራዎች በየጊዜው እየገመገሙ የተጠያቂነት ሥርዓትን መዘርጋት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
በተለይም የትምህርት ዘርፉን በመለወጥ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል፡፡
በምክክር መድረኩ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ምልመላ፣ መረጣና ምደባ ፣ የከፍተኛ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ነጻ የማህበረሰብ አገልግሎት ረቂቅ ሰነድ ለውይይት መነሻነት በከፍተኛ ትምህርት አስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ቀርቧል፡፡
የቀረቡት ረቂቅ ሰነዶችም በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉ ሪፎርሞች የሚሄዱንበትን አቅጣጫ ህጋዊ መሰረት ለማስያዝ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
የቀረበውን ረቂቅ ሰነድ መነሻ በማድረግ የዩኒቭርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎች አንስተው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በምክክር መድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እየተወሰዱ ባሉ የሪፎርም እርምጃዎች ዩኒቨርሲቲዎች ወደፊት ምን አይነት ደረጃ ላይ መድረስ እንዳለባቸው የሚያመላክቱ በመሆኑ የሥራ አመራር ቦርድ አመራሮች ዩኒቨርሲቲዎችን ለመቀየር እየተሄደበት ያለውን ሁኔታ አውቃችሁ በዛ ልክ ኃላፊነታችሁን ልትወጡ ይገባል ብለዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አመራሮ ዩኒቨርሲቲዎች ካላቸው ራዕይና ተልዕኮ አንጻር የሰሯቸውን ሥራዎች በየጊዜው እየገመገሙ የተጠያቂነት ሥርዓትን መዘርጋት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
በተለይም የትምህርት ዘርፉን በመለወጥ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል፡፡
በምክክር መድረኩ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ምልመላ፣ መረጣና ምደባ ፣ የከፍተኛ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ነጻ የማህበረሰብ አገልግሎት ረቂቅ ሰነድ ለውይይት መነሻነት በከፍተኛ ትምህርት አስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ቀርቧል፡፡
የቀረቡት ረቂቅ ሰነዶችም በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉ ሪፎርሞች የሚሄዱንበትን አቅጣጫ ህጋዊ መሰረት ለማስያዝ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
የቀረበውን ረቂቅ ሰነድ መነሻ በማድረግ የዩኒቭርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎች አንስተው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
Mar 13, 2025 64
National News

በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የትምህርት መረጃ አስተዳደር ስርዓትን ወጥና ዲጂታላይዝድ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ።

የትምህርት ሚኒስቴር ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የክልልና ከተማ መስተዳድር የትምህርት መረጃ አስተዳደር ባለሙያዎች፣ ስራ ሀላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሠሩ ባሉ ስራዎች ላይ ምክክር አድርጓል።
በምክክር መድረኩ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ቁልፍ መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ይበልጣል አያሌው የትምህርት ዘርፉን የመረጃ አስተዳደር ስርዓት ለማዘመንና ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው በማያያዝም በመከናወን ላይ ያሉ ጅምር ስራዎችን በሚገባው ፍጥነት በማጠናቀቅ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የመረጃ አስተዳደር ስርዓቱን ማዘመንና ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዘላለም አሰፋ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፉ ያለውን የመረጃ ሥርዓት ለማዘመን እና ዲጂታላይዝ ለማድረግ በርካታ ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን በዚህም መረጃን በሃላፊነት እና በተጠያቂነት በማድረስ ረገድ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማረም ጥረት እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
ከትምህርት ቤት ጀምሮ ያለውን የመረጃ ስርዓት በማዘመን፣ ጥራትና ታዓማኒነቱን በማስጠበቅ በወቅቱ ተደራሽ ለማድረግና ጥቅም ላይ ማዋል የሚደረገውን ጥረት ባለድርሻ አካላት እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።
የትምህርት መረጃ አስተዳደር ስርዓትና የአይሲቲ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰብስብ ለማ በበኩላቸው በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች የመረጃ ስርዓቱን ወጥና ዲጂታላይዝድ በማድረግ በመረጃ አሰባሰብ አደረጃጀትና ትንተና ተደራሽነትን ለማሳደግ ያስችላል ብለዋል።
በምክክር መድረኩ መረጃ ኦን ላይን (online) ብቻ ሳይሆን ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ኦፍ ላይን (Off line ) እና በሌሎችም አማራጮች በቴክኖሎጂ እንዴት መጠቀምና ሪፖርት ማድረግ እንደሚቻል መመላከቱንም አቶ ሰብስብ ለማ አመላክተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የክልልና ከተማ መስተዳድር የትምህርት መረጃ አስተዳደር ባለሙያዎች፣ ስራ ሀላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሠሩ ባሉ ስራዎች ላይ ምክክር አድርጓል።
በምክክር መድረኩ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ቁልፍ መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ይበልጣል አያሌው የትምህርት ዘርፉን የመረጃ አስተዳደር ስርዓት ለማዘመንና ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው በማያያዝም በመከናወን ላይ ያሉ ጅምር ስራዎችን በሚገባው ፍጥነት በማጠናቀቅ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የመረጃ አስተዳደር ስርዓቱን ማዘመንና ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዘላለም አሰፋ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፉ ያለውን የመረጃ ሥርዓት ለማዘመን እና ዲጂታላይዝ ለማድረግ በርካታ ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን በዚህም መረጃን በሃላፊነት እና በተጠያቂነት በማድረስ ረገድ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማረም ጥረት እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
ከትምህርት ቤት ጀምሮ ያለውን የመረጃ ስርዓት በማዘመን፣ ጥራትና ታዓማኒነቱን በማስጠበቅ በወቅቱ ተደራሽ ለማድረግና ጥቅም ላይ ማዋል የሚደረገውን ጥረት ባለድርሻ አካላት እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።
የትምህርት መረጃ አስተዳደር ስርዓትና የአይሲቲ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰብስብ ለማ በበኩላቸው በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች የመረጃ ስርዓቱን ወጥና ዲጂታላይዝድ በማድረግ በመረጃ አሰባሰብ አደረጃጀትና ትንተና ተደራሽነትን ለማሳደግ ያስችላል ብለዋል።
በምክክር መድረኩ መረጃ ኦን ላይን (online) ብቻ ሳይሆን ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ኦፍ ላይን (Off line ) እና በሌሎችም አማራጮች በቴክኖሎጂ እንዴት መጠቀምና ሪፖርት ማድረግ እንደሚቻል መመላከቱንም አቶ ሰብስብ ለማ አመላክተዋል።
Mar 07, 2025 1.1K
National News

ዩኒቨርሲቲዎች ነፃ ምሁራዊ ውይይት የሚካሄድባቸው የሀገር የሀሳብና የእውቀት መሪ ሊሆኑ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ አሳሰቡ።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ አመራሮችና ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች ተልዕኳቸውን በሚገባ እንዲወጡ ከመንደር አስተሳሰብና ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች በነፃነት እውነተኛ ምሁራዊ ውይይት የሚደረግባቸው የዚች ሀገር እውቀት መሪ ሊሆኑ ይገባል፤ ወደዛ እንዲሄዱም እንፈልጋለን ያሉ ሲሆን፤
ዩኒቨርሲቲዎች ትክክልና ስህተትን የሚለዩ ጥሩ ሥነ-ምግባር የተላበሱ ምሩቃንን የሚያፈሩ እንዲሁም ሙስናን የሚቃወሙና የሚከላከሉ ሊሆኑም እንደሚገባም አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ሪሶርስ በአግባቡ ለመጠቀም የቅድሚያ ትኩረት ጉዳዮችን ለይተው በመስራት ችግሮችን ደረጃ በደረጃ መፍታት ይጠበቅባቸዋል ፤
በዚህም አዲሱ አመራር የትምህርት ጥራት የሚያረጋግጡ ሥራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይኖርበታልም ብለዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ(ዶ/ር) በተቋሙ የታዩ ጠንካራና መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች ለውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የዩኒቨርስቲው አዲስ አመራሮች ተቋሙን ካለበት ችግር ለማውጣት ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው አብራርተዋል።
የዩኒቨርስቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ታደሰ ረጋሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋሙን ለመለወጥ ከሁሉም አመራርና በለድርሻ ጋር በመግባባት ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልፀዋል።
የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላትም የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የአመራር ለውጥ ከተደረገላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ አመራሮችና ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች ተልዕኳቸውን በሚገባ እንዲወጡ ከመንደር አስተሳሰብና ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች በነፃነት እውነተኛ ምሁራዊ ውይይት የሚደረግባቸው የዚች ሀገር እውቀት መሪ ሊሆኑ ይገባል፤ ወደዛ እንዲሄዱም እንፈልጋለን ያሉ ሲሆን፤
ዩኒቨርሲቲዎች ትክክልና ስህተትን የሚለዩ ጥሩ ሥነ-ምግባር የተላበሱ ምሩቃንን የሚያፈሩ እንዲሁም ሙስናን የሚቃወሙና የሚከላከሉ ሊሆኑም እንደሚገባም አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ሪሶርስ በአግባቡ ለመጠቀም የቅድሚያ ትኩረት ጉዳዮችን ለይተው በመስራት ችግሮችን ደረጃ በደረጃ መፍታት ይጠበቅባቸዋል ፤
በዚህም አዲሱ አመራር የትምህርት ጥራት የሚያረጋግጡ ሥራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይኖርበታልም ብለዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ(ዶ/ር) በተቋሙ የታዩ ጠንካራና መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች ለውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የዩኒቨርስቲው አዲስ አመራሮች ተቋሙን ካለበት ችግር ለማውጣት ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው አብራርተዋል።
የዩኒቨርስቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ታደሰ ረጋሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋሙን ለመለወጥ ከሁሉም አመራርና በለድርሻ ጋር በመግባባት ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልፀዋል።
የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላትም የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የአመራር ለውጥ ከተደረገላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
Mar 07, 2025 1K
National News

የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነቱን ለማረጋገጥ የሚካሄዱ ስራዎች የሁሉንም የልማት አጋሮችና ባለድርሻዎች የጋራ ተሳትፎና ርብርብ እንደሚጠይቁ ተጠቆመ፤ የሂዩማን ካፒታል (Human Capital) ፕሮጀክት መክፈቻና ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በትምህርት ሚኒስትር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነቱን ለማረጋገጥ የሁሉንም የልማት አጋሮችና ባለድርሻዎች ቅንጅት ፣ ተሳትፎና ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት ትምህርትን ለማዳረስ በተሰሩ ስራዎች የተሻለ አፈፃፀም ቢኖርም የትምህርት ጥራትን ከማረጋገጥ አኳያ አሁንም ሰፊ ክፍተት መኖሩን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ተናግረዋል።፡
በትምህርት ለትውልድ መርሃ ግብር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሳደግ፣ የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማትና ሌሎችም አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ስፋትና ጥልቀት ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል።
የሁዩማን ካፒታልረ ፕሮጀክቱ በ65 ወረዳወች እንደሚተገበር የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ፕሮጀክቱን በመደገፍ ላይ ለሚገኙት የገንዘብ ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የዓለም ባንክና ለሌሎችም ባለድርሻዎች ምስጋና አቅርበዋል።፡
በመድረኩ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በሚካሄድባቸው ወረዳዎች የሚፈለገው ውጤት እንዲመዘገብ በትኩረትና በውጤታማነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዓለም ባንክ የፕሮጀክቱ ቲም ሊደር የሆኑት ሚስተር ሳመር ኤ አይ ሳመራይ በበኩላቸው የዓለም ባንክ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ለሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በመርሃ ግበብሩ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ፣ሴክተር መስሪያ ቤቶች የስራ ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙዎች ፣ ከዓለም ባንክና ከ65 ወረዳዎች የተወከሉ ተሳታፊዎች ተገኘተዋል።
በትምህርት ሚኒስትር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነቱን ለማረጋገጥ የሁሉንም የልማት አጋሮችና ባለድርሻዎች ቅንጅት ፣ ተሳትፎና ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት ትምህርትን ለማዳረስ በተሰሩ ስራዎች የተሻለ አፈፃፀም ቢኖርም የትምህርት ጥራትን ከማረጋገጥ አኳያ አሁንም ሰፊ ክፍተት መኖሩን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ተናግረዋል።፡
በትምህርት ለትውልድ መርሃ ግብር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሳደግ፣ የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማትና ሌሎችም አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ስፋትና ጥልቀት ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል።
የሁዩማን ካፒታልረ ፕሮጀክቱ በ65 ወረዳወች እንደሚተገበር የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ፕሮጀክቱን በመደገፍ ላይ ለሚገኙት የገንዘብ ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የዓለም ባንክና ለሌሎችም ባለድርሻዎች ምስጋና አቅርበዋል።፡
በመድረኩ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በሚካሄድባቸው ወረዳዎች የሚፈለገው ውጤት እንዲመዘገብ በትኩረትና በውጤታማነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዓለም ባንክ የፕሮጀክቱ ቲም ሊደር የሆኑት ሚስተር ሳመር ኤ አይ ሳመራይ በበኩላቸው የዓለም ባንክ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ለሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በመርሃ ግበብሩ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ፣ሴክተር መስሪያ ቤቶች የስራ ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙዎች ፣ ከዓለም ባንክና ከ65 ወረዳዎች የተወከሉ ተሳታፊዎች ተገኘተዋል።
Mar 06, 2025 1.1K
Recent News
Follow Us