News

National News

የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅርቦት ለማሻሻል አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም በመጪው የትምህርት ዘመን እንደሚተገበር ተገለጸ።

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅርቦት ለማሻሻል በ2018 ዓ.ም አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም በ6 ዩኒቨርስቲዎች ተግባራዊ ይደረጋል።
‎የመርሃ ግብሩ ዓላማ የመምህራንን አጠቃላይ አቅርቦት በማሻሻል ረገድ የሚስተዋሉ እጥረቶችና የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት መሆኑንም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል።
‎በአማራጭ የመምህራን የትምህርት መርሃ ግብሩ ከምሁራን ጋር የተመከረበት ፣ በየደረጃው የሚገኙ መምህራንና ሌሎችም የዘርፉ ባለድርሻዎችና ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በውይይት ከዳበረ በኋላ መጽደቁን አብራርተዋል።
‎አማራጭ የመምህራን ትምህርት መርሃ ግብሩ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲተገበር ከአሁን በፊት በትምህርት ዙሪያ በትኩረት እንዲሰሩ በተለዩ 6 ዩኒቨርስቲዎችና ክልሎች መላኩን ጠቁመዋል።
‎ከሁለተኛ ደረጃ መምህራን አቅርቦት ባሻገርም በቅድመ አንደኛ ደረጃ ላይ ያለውን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል ፕሮግራሙ እንደ አንድ አማራጭ እንዲወሰድ ፍሬም ዎርኩ ለክልሎች እንዲደርስ መደረጉንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ጨምረው ተናግረዋል።
‎የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራሙ የመምህራንን አቅርቦት ለማሳደግ የሚያስችል አማራጭ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎ፕሮግራሙ በመጪው የትምህርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ በትምህርት ላይ በሚሰሩ 6ቱ ዩኒቨርስቲዎች የሚተገበር ቢሆንም ውጤቱ እየታየ እየተሻሻለና እየዳበረ እንደሚሄድም ሃላፊው አክለው ገልጸዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅርቦት ለማሻሻል በ2018 ዓ.ም አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም በ6 ዩኒቨርስቲዎች ተግባራዊ ይደረጋል።
‎የመርሃ ግብሩ ዓላማ የመምህራንን አጠቃላይ አቅርቦት በማሻሻል ረገድ የሚስተዋሉ እጥረቶችና የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት መሆኑንም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል።
‎በአማራጭ የመምህራን የትምህርት መርሃ ግብሩ ከምሁራን ጋር የተመከረበት ፣ በየደረጃው የሚገኙ መምህራንና ሌሎችም የዘርፉ ባለድርሻዎችና ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በውይይት ከዳበረ በኋላ መጽደቁን አብራርተዋል።
‎አማራጭ የመምህራን ትምህርት መርሃ ግብሩ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲተገበር ከአሁን በፊት በትምህርት ዙሪያ በትኩረት እንዲሰሩ በተለዩ 6 ዩኒቨርስቲዎችና ክልሎች መላኩን ጠቁመዋል።
‎ከሁለተኛ ደረጃ መምህራን አቅርቦት ባሻገርም በቅድመ አንደኛ ደረጃ ላይ ያለውን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል ፕሮግራሙ እንደ አንድ አማራጭ እንዲወሰድ ፍሬም ዎርኩ ለክልሎች እንዲደርስ መደረጉንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ጨምረው ተናግረዋል።
‎የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራሙ የመምህራንን አቅርቦት ለማሳደግ የሚያስችል አማራጭ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎ፕሮግራሙ በመጪው የትምህርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ በትምህርት ላይ በሚሰሩ 6ቱ ዩኒቨርስቲዎች የሚተገበር ቢሆንም ውጤቱ እየታየ እየተሻሻለና እየዳበረ እንደሚሄድም ሃላፊው አክለው ገልጸዋል።
Jul 24, 2025 130
National News

የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ብቃትና ተነሳሽነት ለትምህርት ጥራት ወሳኝ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ አስገነዘቡ፤

ከመጪው ሐምሌ 28 ጀምሮ ከ84 ሺ በላይ ለሚሆኑ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ልዩ የክረምት የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገለጸ።
‎የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ የተጀመረውን የአሰልጣኞች ስልጠና ሲከፍቱ እንደገለጹት የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃትና ተነሳሽነት ማሳደግ ለትምህርት ጥራት ወሳኝ መሆኑን አስታውቀዋል።
መምህርነት ዜጋን በዕውቀት፣ በክህሎትና በሥነምግባር በማነጽ ተምህርት የሚያስጨብጥና ዜጎች ችግር ፈቺ ፣ተመራማሪ፣ ሀገር ተረካቢና ገንቢ እንዲሆኑ የሚቀርጽ ሙያ መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎መምህርነት ቅድመ ሁኔታዎች ሳይገድቡት የወላጅነትና የባለአደራነት ሚና የሚወጣ የሙያዎች ሁሉ ቁንጮ በመሆኑ መምህራን የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት እንዲወጡና የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል የትምህርት ቤት አመራሮቾ ከፍተኛ ድርሻ አላቸው ብለዋል።
‎የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሥርዓተ ትምህርት ፣በመምህራንና አመራሮች ልማት፣ትምህርት ቤቶችን ምቹ በማድረግና ሌሎች በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃት ለማሳደግ ባለፈው ዓመት በተሰጠው ስልጠና ከተወሰዱ ልምዶች በመነሳት የታዩ ክፍተቶችን ሊቀርፉ የሚችሉ ስልቶችን በመንደፍ ከመጪው ሐምሌ 28 ጀምሮ ለ2ኛ ጊዜ ከ84 ሺ ለሚበልጡ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና እንደሚሰጥ የገለፁ ሲሆን የዛሬው የአሰልጣኞች ስልጠና መርሃ ግብር ተሳታፊዎችም የተጣለባቸውን ትልቅ አገራዊ ተልዕኮ በብቃት እንዲወጡም የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
‎የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ብርሃነ መስቀል ጠና በበኩላቸው የትምህርት ስብራትን ለማከምና ትውልድን ለማነጽ መምህራን ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።
‎የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በበኩላቸው የአሰልጣኞች ስልጠናው ዓላማ የመምህራንንና የትምህርት አመራሮችን አቅምና ብቃት በማሳደግ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና ለሁለተኛ ጊዜ መዘጋጀቱን ጠቁመው ባለፈው ዓመት የተሰጠው ስልጠና ጠቃሚ ልምድና ተሞክሮ መገኘቱንም አብራርተዋል።
‎ዛሬ በተጀመረውና ለሦስት ቀናት በሚቆየው ልዩ የክረምት መምህራንና የትምህርት አመራሮች የአሰልጣኞች ስልጠና ከ30 ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ 630 ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።
ከመጪው ሐምሌ 28 ጀምሮ ከ84 ሺ በላይ ለሚሆኑ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ልዩ የክረምት የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገለጸ።
‎የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ የተጀመረውን የአሰልጣኞች ስልጠና ሲከፍቱ እንደገለጹት የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃትና ተነሳሽነት ማሳደግ ለትምህርት ጥራት ወሳኝ መሆኑን አስታውቀዋል።
መምህርነት ዜጋን በዕውቀት፣ በክህሎትና በሥነምግባር በማነጽ ተምህርት የሚያስጨብጥና ዜጎች ችግር ፈቺ ፣ተመራማሪ፣ ሀገር ተረካቢና ገንቢ እንዲሆኑ የሚቀርጽ ሙያ መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎መምህርነት ቅድመ ሁኔታዎች ሳይገድቡት የወላጅነትና የባለአደራነት ሚና የሚወጣ የሙያዎች ሁሉ ቁንጮ በመሆኑ መምህራን የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት እንዲወጡና የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል የትምህርት ቤት አመራሮቾ ከፍተኛ ድርሻ አላቸው ብለዋል።
‎የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሥርዓተ ትምህርት ፣በመምህራንና አመራሮች ልማት፣ትምህርት ቤቶችን ምቹ በማድረግና ሌሎች በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃት ለማሳደግ ባለፈው ዓመት በተሰጠው ስልጠና ከተወሰዱ ልምዶች በመነሳት የታዩ ክፍተቶችን ሊቀርፉ የሚችሉ ስልቶችን በመንደፍ ከመጪው ሐምሌ 28 ጀምሮ ለ2ኛ ጊዜ ከ84 ሺ ለሚበልጡ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና እንደሚሰጥ የገለፁ ሲሆን የዛሬው የአሰልጣኞች ስልጠና መርሃ ግብር ተሳታፊዎችም የተጣለባቸውን ትልቅ አገራዊ ተልዕኮ በብቃት እንዲወጡም የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
‎የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ብርሃነ መስቀል ጠና በበኩላቸው የትምህርት ስብራትን ለማከምና ትውልድን ለማነጽ መምህራን ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።
‎የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በበኩላቸው የአሰልጣኞች ስልጠናው ዓላማ የመምህራንንና የትምህርት አመራሮችን አቅምና ብቃት በማሳደግ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና ለሁለተኛ ጊዜ መዘጋጀቱን ጠቁመው ባለፈው ዓመት የተሰጠው ስልጠና ጠቃሚ ልምድና ተሞክሮ መገኘቱንም አብራርተዋል።
‎ዛሬ በተጀመረውና ለሦስት ቀናት በሚቆየው ልዩ የክረምት መምህራንና የትምህርት አመራሮች የአሰልጣኞች ስልጠና ከ30 ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ 630 ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።
Jul 23, 2025 88
National News

ኢትዮጵያና አልጄሪያ በትምህርትና ስልጠና መስክ ያላቸውን ትብብር ሊያሳድጉ እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር መሀመድ ካሊድን በ/ጽቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡
ሚንስትሩ ከአምባሰደሩ ጋር በነበራቸው ቆይታ እየተለወጠ ባለው የአለም ስርዓት ውስጥ አፍሪካውያን ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባቸው የገለጹ ሲሆን በትምህርት ዘርፍ ከአልጄሪያ ጋር በትብብር ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት ገልጸዋል፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ ከዚሁ ጋር አያይዘው ባረጉት ገለጻ በኢትዮጵያና አልጄሪያ መካል ያለውን የትምህርትና ስልጠና ትብብር ከማጠናከር ባለፈ በሀገራቱ የጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ምርምሮችን በጋራ ለመስራት ፣የመምህራንና ተማሪዎች ልውውጥ ለማድረግ ፣ የነጻ ትምህርት እድሎችን ለማመቻቸት እንዲሁም የቴክክና ሙያ ትምህርት አሰልጣኞች ስልጠና ላይ አብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ዶ/ር መሀመድ ካሊድ በበኩላቸው ኢትዮጵና አልጀሪያ በቀጠናዊና አለማቀፋዊ የገራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ትብብር ያላቸው መሆኑን የገለጹ ሲሆን ይህን ዘርፈ ብዙ ትብብር ማስፋትና ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
አምባሳደሩ በማያያዝ እንደገለጹት የአልጄሪያ መንግስት በኢትዮያ በኩል የሚቀርብለትን የትብብር ፍላጎት መሰረት በማድረግ ስምምነት የመፈራረምና አብሮ የመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር መሀመድ ካሊድን በ/ጽቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡
ሚንስትሩ ከአምባሰደሩ ጋር በነበራቸው ቆይታ እየተለወጠ ባለው የአለም ስርዓት ውስጥ አፍሪካውያን ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባቸው የገለጹ ሲሆን በትምህርት ዘርፍ ከአልጄሪያ ጋር በትብብር ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት ገልጸዋል፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ ከዚሁ ጋር አያይዘው ባረጉት ገለጻ በኢትዮጵያና አልጄሪያ መካል ያለውን የትምህርትና ስልጠና ትብብር ከማጠናከር ባለፈ በሀገራቱ የጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ምርምሮችን በጋራ ለመስራት ፣የመምህራንና ተማሪዎች ልውውጥ ለማድረግ ፣ የነጻ ትምህርት እድሎችን ለማመቻቸት እንዲሁም የቴክክና ሙያ ትምህርት አሰልጣኞች ስልጠና ላይ አብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ዶ/ር መሀመድ ካሊድ በበኩላቸው ኢትዮጵና አልጀሪያ በቀጠናዊና አለማቀፋዊ የገራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ትብብር ያላቸው መሆኑን የገለጹ ሲሆን ይህን ዘርፈ ብዙ ትብብር ማስፋትና ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
አምባሳደሩ በማያያዝ እንደገለጹት የአልጄሪያ መንግስት በኢትዮያ በኩል የሚቀርብለትን የትብብር ፍላጎት መሰረት በማድረግ ስምምነት የመፈራረምና አብሮ የመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
Jul 23, 2025 76
National News

"ለትውልድ ስንል አረንጎዴ አሻራችንን ያለልዩነት እናስቀምጣለን" የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሸገር ከተማ አካሄዱ።
"በመትከል ማንሠራራት" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የአረንጎዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉት የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ለትውልድ ስንል አረንጓዴ አሻራችንን ያለልዩነት እናስቀምጣለን ብለዋል።
ሚንስትሩ ከዚሁ ጋር በማያያዝ ባስተላለፉት መልእክት ሀገርና ትውልድን በሚጠቅሙ ጉዳዬች ላይ ሁሉም ዜጋ ያለልዩነት የበኩሉን አስተዋጾ ማድረግ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
በኢፋ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የተከናወነው የችግኝ ተከላ ከስራና ሙያ ጋር የተያዘና ለተማሪዎች አርያ ለመሆን ታስቦ መሆኑን የገለጹትት ሚንስትሩ ሁሉም ዜጋ ባለው የሙያም ይሁን ማህበራዊ ትስስር ሁሌም አረንጓዴ አሻራውን ማኖር አለበት ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ሀገራችን እያከናወነች ያለው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሌሎች ሀገራት ልምድ የሚቀስሙበት መሆኑን የገለጹ ሲሆን ልማቱ የተፈጥሮ ሚዛንን ከማስጠበቅ ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ጭምር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ለጋዜጠኞች በሠጡት ማብራሪያ ገልጸዋል።
አረንጓዴ አሻራን ማኖር አገራችን ኢትዮጵያን ወደፊት የሚወስድና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ዋነኛ ተግባር በመሆኑ የሁልጊዜ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ሚንስትር ዴኤታዋ አያይዘው ገልጸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለትውልድ ምቹና ተስማሚ ሀገር ለማስረከብ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል።
መርሃ ግብሩ የአረንጎዴ አሻራ የሁሉም ነገር መሠረት ስለመሆኑ እንዲሁም አገርን ለማበልጸግና ወደፊት ለማሻገር ቁልፍ ሚና ያለው ስለመሆኑ ግንዛቤ የተፈጠረበት ነው።
በመርሐ ግብሩ የትምህርት ሚኒስቴር ፣ የኢትዮጵይ ትምህርት ባለስልጣን እንዲሁም የአገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
 
የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሸገር ከተማ አካሄዱ።
"በመትከል ማንሠራራት" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የአረንጎዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉት የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ለትውልድ ስንል አረንጓዴ አሻራችንን ያለልዩነት እናስቀምጣለን ብለዋል።
ሚንስትሩ ከዚሁ ጋር በማያያዝ ባስተላለፉት መልእክት ሀገርና ትውልድን በሚጠቅሙ ጉዳዬች ላይ ሁሉም ዜጋ ያለልዩነት የበኩሉን አስተዋጾ ማድረግ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
በኢፋ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የተከናወነው የችግኝ ተከላ ከስራና ሙያ ጋር የተያዘና ለተማሪዎች አርያ ለመሆን ታስቦ መሆኑን የገለጹትት ሚንስትሩ ሁሉም ዜጋ ባለው የሙያም ይሁን ማህበራዊ ትስስር ሁሌም አረንጓዴ አሻራውን ማኖር አለበት ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ሀገራችን እያከናወነች ያለው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሌሎች ሀገራት ልምድ የሚቀስሙበት መሆኑን የገለጹ ሲሆን ልማቱ የተፈጥሮ ሚዛንን ከማስጠበቅ ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ጭምር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ለጋዜጠኞች በሠጡት ማብራሪያ ገልጸዋል።
አረንጓዴ አሻራን ማኖር አገራችን ኢትዮጵያን ወደፊት የሚወስድና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ዋነኛ ተግባር በመሆኑ የሁልጊዜ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ሚንስትር ዴኤታዋ አያይዘው ገልጸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለትውልድ ምቹና ተስማሚ ሀገር ለማስረከብ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል።
መርሃ ግብሩ የአረንጎዴ አሻራ የሁሉም ነገር መሠረት ስለመሆኑ እንዲሁም አገርን ለማበልጸግና ወደፊት ለማሻገር ቁልፍ ሚና ያለው ስለመሆኑ ግንዛቤ የተፈጠረበት ነው።
በመርሐ ግብሩ የትምህርት ሚኒስቴር ፣ የኢትዮጵይ ትምህርት ባለስልጣን እንዲሁም የአገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
 
Jul 22, 2025 128
National News

የትምህርት ሚኒስቴር የሚያስገነባቸውን የፌዴራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን ስራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።

በአዲሱ የትምህርት ዘመን ትምህርት ሚኒስቴር እያስገነባቸው ካሉ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል የተወሰኑት በመጪው የትምህርት ዘመን ስራ እንደሚጀምሩ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞ በሰጡት ማብራሪያ እንዳስታወቁት በሳይንስና በቴክኖሎጂ የበቁ የነገ የዚች ሀገር መሪ መሆን የሚችሉ ዜጎችን ለማፍራት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቹ ከሁሉም አካባበዎች የሚመጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው፣ አብሮ መኖርና ማደግን የሚለምዱባቸውና የአገሪቱ የወደፊት መሪዎችን የምናፈራባቸው ቦታዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡
በዚህም መነሻ የትምህርት ሚኒስቴር በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች እያስገነባቸው ካሉ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ድረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል የተወሰኑትን በመጪው የትምህርት ዘመን ስራ ለማስጀመር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ከዚህ ቀደም በአገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ ከአርባ የማያንሱ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናዎች ከሞላ ጎደል ሁሉም ተማሪዎችን ማሳለፍ መቻላቸውንም በአብነት አንስተዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ በተገነቡት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ2017 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍል ካጠናቀቁ ተማሪዎች መካከል መልምሎ ለማስገባት ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን ለዚህም ተማሪዎች ተገቢውን መስፈርት አሟልተው እንዲጠባበቁ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል።
በአዲሱ የትምህርት ዘመን ትምህርት ሚኒስቴር እያስገነባቸው ካሉ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል የተወሰኑት በመጪው የትምህርት ዘመን ስራ እንደሚጀምሩ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞ በሰጡት ማብራሪያ እንዳስታወቁት በሳይንስና በቴክኖሎጂ የበቁ የነገ የዚች ሀገር መሪ መሆን የሚችሉ ዜጎችን ለማፍራት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቹ ከሁሉም አካባበዎች የሚመጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው፣ አብሮ መኖርና ማደግን የሚለምዱባቸውና የአገሪቱ የወደፊት መሪዎችን የምናፈራባቸው ቦታዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡
በዚህም መነሻ የትምህርት ሚኒስቴር በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች እያስገነባቸው ካሉ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ድረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል የተወሰኑትን በመጪው የትምህርት ዘመን ስራ ለማስጀመር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ከዚህ ቀደም በአገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ ከአርባ የማያንሱ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናዎች ከሞላ ጎደል ሁሉም ተማሪዎችን ማሳለፍ መቻላቸውንም በአብነት አንስተዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ በተገነቡት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ2017 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍል ካጠናቀቁ ተማሪዎች መካከል መልምሎ ለማስገባት ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን ለዚህም ተማሪዎች ተገቢውን መስፈርት አሟልተው እንዲጠባበቁ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል።
Jul 17, 2025 531
National News

የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከባለፉት ሶስት አመታት በተሻለ መልኩ በሠላም እና በስኬት መጠናቀቁ ተገለጸ።

የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የታለመለትን ግብ በመምታት በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።
ሚንስትሩ የነበረውን የፈተና አሰጣጥ ሂደት አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት ሶስት አመታት በተወሰነ መልኩ ያጋጥሙ የነበሩ የጸጥታ ችግሮች፣ የፈተና ስርቆት ሙከራዎች፣ የፈተና ስርዓትና አስተዳደር የዲሲፒሊን ግድፈቶች በዘንድሮው አመት ቀንሰው መገኘታቸውን አብራርተዋል።
ለዚህም የበይነ መረብ የፈተና ሽፋን በአንድ አመት ውስጥ በአራት እጥፍ ማደጉ፤የፈተና ግብረ ሀይሉ ያልተቆጠበ ጥረት፤ እንዲሁም ተማሪዎች ሰርቶ ውጤት ማምጣት አማራጭ የሌለው መፍትሄ መሆኑን መገንዘባቸውና መሰል ለውጦች ችግሮች ጎልተው እንዳይስተዋሉ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ተናግረዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናው በአራት ዙሮች እንዲሠጥ የተደረገ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በአራቱም ዙሮች የተሰጡ ፈተናዎች ተቀራራቢ (አቻ) መሆናቸውን አብራርተዋል።
በ2017 የትምህርት ዘመን በአጠቃላይ ከተመዘገቡ ተፈታኞች 608,742 መካከል 581,905 (95.6%) ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 134,828 (23.2%) በበይነ መረብ ብቻ የተፈተኑ መሆናቸው ተብራርቷል።
ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በአማራ ብሔራዊ ክልል ያሉ እና የተወሰኑ የህግ ታራሚዎች በድምሩ 4,966 ተፈታኞች ከነሐሴ 26-28/2017 ዓ/ም በሁለተኛ ዙር የተዘጋጀላቸውን ፈተና በወረቀት የሚወስዱ መሆኑንም አያይዘው አሳውቀዋል።
በ2016 የትምህርት ዘመን በበይነ መረብ የተፈተኑ ተፈታኞች ቁጥር 29,727 ብቻ የነበረ ሲሆን በዘንድሮ አመት ወደ 134,825 መድረሱ ከፍተኛ ስኬት መሆኑ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተብራርቷል።
በመጨረሻም በፈተና አሰጣጥና አስተዳደር ሂደት ውስጥ የድርሻቸውን ላበረከቱ ሁለ የትምህርት ሚኒስቴር ልባዊ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ ብሏል።
የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የታለመለትን ግብ በመምታት በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።
ሚንስትሩ የነበረውን የፈተና አሰጣጥ ሂደት አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት ሶስት አመታት በተወሰነ መልኩ ያጋጥሙ የነበሩ የጸጥታ ችግሮች፣ የፈተና ስርቆት ሙከራዎች፣ የፈተና ስርዓትና አስተዳደር የዲሲፒሊን ግድፈቶች በዘንድሮው አመት ቀንሰው መገኘታቸውን አብራርተዋል።
ለዚህም የበይነ መረብ የፈተና ሽፋን በአንድ አመት ውስጥ በአራት እጥፍ ማደጉ፤የፈተና ግብረ ሀይሉ ያልተቆጠበ ጥረት፤ እንዲሁም ተማሪዎች ሰርቶ ውጤት ማምጣት አማራጭ የሌለው መፍትሄ መሆኑን መገንዘባቸውና መሰል ለውጦች ችግሮች ጎልተው እንዳይስተዋሉ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ተናግረዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናው በአራት ዙሮች እንዲሠጥ የተደረገ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በአራቱም ዙሮች የተሰጡ ፈተናዎች ተቀራራቢ (አቻ) መሆናቸውን አብራርተዋል።
በ2017 የትምህርት ዘመን በአጠቃላይ ከተመዘገቡ ተፈታኞች 608,742 መካከል 581,905 (95.6%) ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 134,828 (23.2%) በበይነ መረብ ብቻ የተፈተኑ መሆናቸው ተብራርቷል።
ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በአማራ ብሔራዊ ክልል ያሉ እና የተወሰኑ የህግ ታራሚዎች በድምሩ 4,966 ተፈታኞች ከነሐሴ 26-28/2017 ዓ/ም በሁለተኛ ዙር የተዘጋጀላቸውን ፈተና በወረቀት የሚወስዱ መሆኑንም አያይዘው አሳውቀዋል።
በ2016 የትምህርት ዘመን በበይነ መረብ የተፈተኑ ተፈታኞች ቁጥር 29,727 ብቻ የነበረ ሲሆን በዘንድሮ አመት ወደ 134,825 መድረሱ ከፍተኛ ስኬት መሆኑ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተብራርቷል።
በመጨረሻም በፈተና አሰጣጥና አስተዳደር ሂደት ውስጥ የድርሻቸውን ላበረከቱ ሁለ የትምህርት ሚኒስቴር ልባዊ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ ብሏል።
Jul 16, 2025 389
National News

የ2017 ትምህርት ዘመንየ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ሀገር አቀፍ ፈተና ተጠናቀቀ።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ትምህርት ዘመን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና መጠናቀቁን ተገልጿል።
ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8/ 2017 ዓ.ም በመላ አገሪቱ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡
ከዝግጅት ጀምሮ በፈተናው ወቅት በየደረጃው የሚገኙ በፈተናው ስራ የተሳተፉ ባለሙያዎች ፣ አመራሮችና ባለድርሻዎች በፈተናው ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጋቸው ፈተናው በሰላም ተጠናቋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የፈተናው ስራ እንዲሳካ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለተወጡ ኃላፊዎች፣ አስተባባሪዎች፣ ፈታኞች፣ የጸጥታ አስከባሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻዎች ላበረከቱት አስዋጽኦ ምስጋና ያቀርባል፡፡
ተፈታኞችም ፈተናው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ላሳዩት በጎ ስነ- ምግባር አያመሰገነ መልካም እድል እንዲገጥማቸው ትምህርት ሚኒስቴር ምኞቱን ይገልጻል፡፡
የ2017 ትምህርት ዘመን ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ በወረቀትና በበይነ መረብ በመላ ሀገሪቱ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል።

 

በአገር አቀፍ ደረጃ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ትምህርት ዘመን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና መጠናቀቁን ተገልጿል።
ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8/ 2017 ዓ.ም በመላ አገሪቱ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡
ከዝግጅት ጀምሮ በፈተናው ወቅት በየደረጃው የሚገኙ በፈተናው ስራ የተሳተፉ ባለሙያዎች ፣ አመራሮችና ባለድርሻዎች በፈተናው ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጋቸው ፈተናው በሰላም ተጠናቋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የፈተናው ስራ እንዲሳካ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለተወጡ ኃላፊዎች፣ አስተባባሪዎች፣ ፈታኞች፣ የጸጥታ አስከባሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻዎች ላበረከቱት አስዋጽኦ ምስጋና ያቀርባል፡፡
ተፈታኞችም ፈተናው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ላሳዩት በጎ ስነ- ምግባር አያመሰገነ መልካም እድል እንዲገጥማቸው ትምህርት ሚኒስቴር ምኞቱን ይገልጻል፡፡
የ2017 ትምህርት ዘመን ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ በወረቀትና በበይነ መረብ በመላ ሀገሪቱ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል።
Jul 15, 2025 487
National News

ማስታወቂያ

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ ለተማሪዎችና ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን

 

 

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ ለተማሪዎችና ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን

 

 

Jul 11, 2025 885
National News

ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በትምህርቱ ዘርፍ ያላትን ትብብር አጠናክራ መቀጠል እንደምትፈልግ ተገለጸ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር Mr.Monday የተመራ የልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር የቆየ ግንኙነት በተለይም በትምህርቱ ዘርፉ ጠንካራ ትብብር እንደነበራት ጠቅሰው አሁን ኢትዮጵያ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትኩረት በመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም እርምጃዎችን አብራርተዋል።

የደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር Mr.Monday በበኩላቸው ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት እንደነበራት አንስተው ይህንን ታሪካዊ ግንኙነት ሀገራቸው የበለጠ አጠናክረው መቀጠል እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

አክለውም በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ነጻ የትምህርት እድል አግኝተው ከተመረቁ ተማሪዎች መካከል 200 የሚሆኑት በሀገራቸው መንግስት በተለያዩ ቦታዎች ተቀጥረው አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል የምትሰጣቸው ደቡብ ሱዳናውያንን በሚመለከት፣ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርስቲ የሚደረግ ትብብር፣ በጋራ የሚሰሩ ጥናትና ምርምር ሥራዎች እንዲሁም ለደቡብ ሱዳን የትምህርት ሚኒስቴር እና ለከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የአቅም ግንባታ ሥልጠናና ድጋፍ በሚደረግባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በመድረኩም በኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል ያገኙ ደቡብ ሱዳናውያን ከመኝታ፣ ከምግብ  እንዲሁም ከኢሚግሬሽን ጋር ተያይዞ ያሉ ወጪዎች በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈነው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተጠቅሷል።

በመጨረሻም ክቡር ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን ተገኝተው ጉብኝት እንዲያደርጉ የደቡብ/ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋብዘዋቸዋል።

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ ለተማሪዎችና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን

በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር የቆየ ግንኙነት በተለይም በትምህርቱ ዘርፉ ጠንካራ ትብብር እንደነበራት ጠቅሰው አሁን ኢትዮጵያ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትኩረት በመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም እርምጃዎችን አብራርተዋል።

የደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር Mr.Monday በበኩላቸው ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት እንደነበራት አንስተው ይህንን ታሪካዊ ግንኙነት ሀገራቸው የበለጠ አጠናክረው መቀጠል እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

አክለውም በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ነጻ የትምህርት እድል አግኝተው ከተመረቁ ተማሪዎች መካከል 200 የሚሆኑት በሀገራቸው መንግስት በተለያዩ ቦታዎች ተቀጥረው አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል የምትሰጣቸው ደቡብ ሱዳናውያንን በሚመለከት፣ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርስቲ የሚደረግ ትብብር፣ በጋራ የሚሰሩ ጥናትና ምርምር ሥራዎች እንዲሁም ለደቡብ ሱዳን የትምህርት ሚኒስቴር እና ለከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የአቅም ግንባታ ሥልጠናና ድጋፍ በሚደረግባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በመድረኩም በኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል ያገኙ ደቡብ ሱዳናውያን ከመኝታ፣ ከምግብ  እንዲሁም ከኢሚግሬሽን ጋር ተያይዞ ያሉ ወጪዎች በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈነው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተጠቅሷል።

በመጨረሻም ክቡር ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን ተገኝተው ጉብኝት እንዲያደርጉ የደቡብ/ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋብዘዋቸዋል።

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ ለተማሪዎችና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን

Jul 11, 2025 375
National News

በአገሪቱ ተመጣጣኝና ፍትሃዊ የትምህርት ዘርፍ ልማትን ለማምጣት እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ፡፡ የትምህርት ቤቶችን ሥርጭት የሚያሳይ የዲጂታል ካርታ የትምህርት ሚኒስትሩ በተገኙበት ይፋ ሆኗል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በሀገሪቱ ተመጣጣኝ የሆነ የትምህርት ዘርፍ ልማትን ለማምጣት ትምህርት ቤቶች ግልጽና ትክክለኛ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ እንዲገነቡ የሚያስችል ዲጅታል የትምህርት ቤቶች ስርጭት የሚያሳይ ካርታ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ባለፉት ዓመታት በነበረው አሰራር የትምህርት ቤቶች ግንባታ ምርጫ የሚወሰነው በገለልተኝነትና በበቂ መረጃ ሳይሆን በዘር ፣ በትውወቅና ፖለቲካዊ ፍላጎትን መሰረት በማድረግ እንደነበረም ፕሮፌሰር ብርሃኑ አስገንዝበዋል፡፡
በመሆኑም በአዲሱ ስርዓት ማንኛውም በኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶችን የመገንባት ፍላጎት ያለው ሰውም ሆነ ለጋሽ ድርጅት የትኛውንም የመንግስት ባለስልጣን ወይም ተጽእኖ ፈጣሪ መጠየቅ ሳያስፈልገው በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርቶ ትምህረት ቤቶችችን መገንባት እንደሚችል አስታውቀዋል፡፡
አክለውም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል የትምህርት እድል ማግኘት እንዳለበት አንስተው ለሁሉም ዜጎች ትምህርትን በፍትሃዊነት ለማድረሰ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትና ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዮሐንስ ወጋሶ( ዶ/ር) በበኩላቸው ይፋ የሆነው የትምህርት ቤቶች ስርጭት ካርታ ከቀበሌ ጀምሮ በየደረጃው የትምህርት ቤቶችን ወቅታዊ ስርጭት፣ የመሰረተ ልማት፣ የህዝብ ብዛት እና ሌሎች መረጃዎችንም አካቶ የያዘ መሆኑ ጠቅሰዋል።
በመሆኑም ለጋሾችም ሆኑ ሌሎች የዘርፉ ባለድርሻዎች መረጃውን በመጠቀም ትምህርት ቤቶችን መገንባትና የድርሻቸውን ማበርከት እንደሚችሉ ገልጸዋል።
በዚህ የትምህርት ስርጭት ካርታ ትምህርት ቤቶቹ የሚገነቡት በተዘጋጀው ስታንዳርድ መሰረት ሲሆን የት ይገነባሉ የሚለውን ምላሽ የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።
በመድረኩ ላይም የትምህርት ልማት ሥራ አጋር የሆኑ የውጪና የሀገር ውስጥ ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በሀገሪቱ ተመጣጣኝ የሆነ የትምህርት ዘርፍ ልማትን ለማምጣት ትምህርት ቤቶች ግልጽና ትክክለኛ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ እንዲገነቡ የሚያስችል ዲጅታል የትምህርት ቤቶች ስርጭት የሚያሳይ ካርታ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ባለፉት ዓመታት በነበረው አሰራር የትምህርት ቤቶች ግንባታ ምርጫ የሚወሰነው በገለልተኝነትና በበቂ መረጃ ሳይሆን በዘር ፣ በትውወቅና ፖለቲካዊ ፍላጎትን መሰረት በማድረግ እንደነበረም ፕሮፌሰር ብርሃኑ አስገንዝበዋል፡፡
በመሆኑም በአዲሱ ስርዓት ማንኛውም በኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶችን የመገንባት ፍላጎት ያለው ሰውም ሆነ ለጋሽ ድርጅት የትኛውንም የመንግስት ባለስልጣን ወይም ተጽእኖ ፈጣሪ መጠየቅ ሳያስፈልገው በትክክለኛ መረጃ ላይ ተመስርቶ ትምህረት ቤቶችችን መገንባት እንደሚችል አስታውቀዋል፡፡
አክለውም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል የትምህርት እድል ማግኘት እንዳለበት አንስተው ለሁሉም ዜጎች ትምህርትን በፍትሃዊነት ለማድረሰ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትና ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዮሐንስ ወጋሶ( ዶ/ር) በበኩላቸው ይፋ የሆነው የትምህርት ቤቶች ስርጭት ካርታ ከቀበሌ ጀምሮ በየደረጃው የትምህርት ቤቶችን ወቅታዊ ስርጭት፣ የመሰረተ ልማት፣ የህዝብ ብዛት እና ሌሎች መረጃዎችንም አካቶ የያዘ መሆኑ ጠቅሰዋል።
በመሆኑም ለጋሾችም ሆኑ ሌሎች የዘርፉ ባለድርሻዎች መረጃውን በመጠቀም ትምህርት ቤቶችን መገንባትና የድርሻቸውን ማበርከት እንደሚችሉ ገልጸዋል።
በዚህ የትምህርት ስርጭት ካርታ ትምህርት ቤቶቹ የሚገነቡት በተዘጋጀው ስታንዳርድ መሰረት ሲሆን የት ይገነባሉ የሚለውን ምላሽ የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።
በመድረኩ ላይም የትምህርት ልማት ሥራ አጋር የሆኑ የውጪና የሀገር ውስጥ ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል።
Jul 10, 2025 293
National News

ዩኒቨርሲቲዎች የተሠጣቸውን ተልዕኮ በሚገባ ለይተው ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ፤ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቦንጋ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች አንድ ጊዜ ከተከፈቱ ተጠያቂነት የለም ማለት አይደለም፦ በተሠጠው ተልዕኮ መሠረት ካልሰሩ የተጠያቂነት ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባል ብለዋል።
በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች በእውነትና እውቀት ለሀገር የሚጠቅም ውይይት የሚደረግባቸው፣ ብቃት ያላቸው የሰው ሃይል ማፍራት የሚችሉ ትክክለኛ ዩኒቨርሳል የሆነ አቋም ሊኖራቸው ይገባል ለዚህም ትኩረት ተሠጥቶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስት ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች አለም አቀፍ እውቀት የሚገበይባቸው ተቋማት በመሆናቸው ተቋማዊ አሰራርን መዘርጋት ተገቢ ነው ለዚህም የዩኒቨርስቲ አመራር ምደባ በእውቀትና በአለም አቀፍ ውድድሮች ሊሆን ይገባል ያሉ ሲሆን
እንደ ሀገር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚሰራው ሥራ የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
በዩኒቨርቲው በተደረገው የሱፐርቪዥን ግኝት መሠረት ሪፖርት ያቀረቡት የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንደር አስተሳሰብ ወጥተው እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
አያይዘውም ዩኒቨርሲቲዎች በእውቀት መመራት መቻል አለባቸው ለዚህም ተቋማቱን ሪፎርም የማድረግ ሥራ እየተሰራ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
አዲሱ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲውን የተሻለ ተወዳዳሪ ለማድረግ ከዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላት ጋር በመወያየት አቅደው እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።
በመድረኩም የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላትም ከአካዳሚክ እና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንስተው በከፍተኛ አመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች አንድ ጊዜ ከተከፈቱ ተጠያቂነት የለም ማለት አይደለም፦ በተሠጠው ተልዕኮ መሠረት ካልሰሩ የተጠያቂነት ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባል ብለዋል።
በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች በእውነትና እውቀት ለሀገር የሚጠቅም ውይይት የሚደረግባቸው፣ ብቃት ያላቸው የሰው ሃይል ማፍራት የሚችሉ ትክክለኛ ዩኒቨርሳል የሆነ አቋም ሊኖራቸው ይገባል ለዚህም ትኩረት ተሠጥቶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስት ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች አለም አቀፍ እውቀት የሚገበይባቸው ተቋማት በመሆናቸው ተቋማዊ አሰራርን መዘርጋት ተገቢ ነው ለዚህም የዩኒቨርስቲ አመራር ምደባ በእውቀትና በአለም አቀፍ ውድድሮች ሊሆን ይገባል ያሉ ሲሆን
እንደ ሀገር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚሰራው ሥራ የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
በዩኒቨርቲው በተደረገው የሱፐርቪዥን ግኝት መሠረት ሪፖርት ያቀረቡት የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንደር አስተሳሰብ ወጥተው እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
አያይዘውም ዩኒቨርሲቲዎች በእውቀት መመራት መቻል አለባቸው ለዚህም ተቋማቱን ሪፎርም የማድረግ ሥራ እየተሰራ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
አዲሱ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲውን የተሻለ ተወዳዳሪ ለማድረግ ከዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላት ጋር በመወያየት አቅደው እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።
በመድረኩም የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላትም ከአካዳሚክ እና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንስተው በከፍተኛ አመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Jul 01, 2025 444
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናን በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው አስጀመሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የሚኒስቴሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ከሾጌ የ2017 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተናን በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው አስጀምረዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ጠንክሮ ያጠና ተማሪ የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በማንሳት ተማሪዎች ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ አበረታተዋል።
የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በዛሬው እለት በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
ዘንድሮ በወረቀትና በበየነ መረብ ከ608 ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሃምሌ 08/2017ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የሚኒስቴሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ከሾጌ የ2017 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተናን በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው አስጀምረዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ጠንክሮ ያጠና ተማሪ የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በማንሳት ተማሪዎች ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ አበረታተዋል።
የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በዛሬው እለት በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
ዘንድሮ በወረቀትና በበየነ መረብ ከ608 ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሃምሌ 08/2017ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል
Jun 30, 2025 332
National News

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን አበረታቱ።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው የከስዓት በኋላ ፈተና አሰጣጥ ሁኔታን ተዘዋውረው በመመልከት ተፈታኝ ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱ ከሥርቆትና ኩረጃ ነፃ ለማድረግ ባለፉት ዓመታት በተሰራው ስራ ለውጥ መምጣቱን በመጥቀስ ተማሪዎች በራሳቸው በመተማመን ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ ምክር ለግሰዋል።
በኩረጃ የሚያልፍ ተማሪ ለራሱም ለሀገሩም አይበጅም ያሉት ሚኒስትሩ ከዚህ በኋላ በዚህ መንገድ የሚገኝ ውጤት አለመኖሩ ግልፅ እየሆነ መጥቷልም ብለዋል።
በዚህም ጠንክሮ ያጠናና የሰራ ተማሪ የተሻለ ውጤት እንደሚያገኝ በመግለፅ ለተማሪዎች መልካም ውጤትን ተመኝተዋል።
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከ608 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸው በወረቀትና በበየነ መረብ እንደሚወስዱ መገለፁ ይታወሳል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው የከስዓት በኋላ ፈተና አሰጣጥ ሁኔታን ተዘዋውረው በመመልከት ተፈታኝ ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱ ከሥርቆትና ኩረጃ ነፃ ለማድረግ ባለፉት ዓመታት በተሰራው ስራ ለውጥ መምጣቱን በመጥቀስ ተማሪዎች በራሳቸው በመተማመን ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ ምክር ለግሰዋል።
በኩረጃ የሚያልፍ ተማሪ ለራሱም ለሀገሩም አይበጅም ያሉት ሚኒስትሩ ከዚህ በኋላ በዚህ መንገድ የሚገኝ ውጤት አለመኖሩ ግልፅ እየሆነ መጥቷልም ብለዋል።
በዚህም ጠንክሮ ያጠናና የሰራ ተማሪ የተሻለ ውጤት እንደሚያገኝ በመግለፅ ለተማሪዎች መልካም ውጤትን ተመኝተዋል።
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከ608 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸው በወረቀትና በበየነ መረብ እንደሚወስዱ መገለፁ ይታወሳል።
Jun 30, 2025 327
National News

የ2017 ዓ.ም. 12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና በመላ አገሪቱ በይነ መረብና በወረቀት ከዛሬ ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል።

ክብርት ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ ፈተናውን በአዲስ አበባ አስጀምረዋል።፡
ክብርት የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ ከተማ እየተሰጠ የሚገኘውን ፈተና በአብርሆት ቤተ መጻህፍት ባስጀመሩበት ውቅት እንደገለጹት ለፈተናው ተገቢው የቅድመ ዝግጅት ስራ ተሰርቷል፡፡
ተማሪዎች አዲሱን ስርኣት ትምህርት መሰረት በማድረግ መጻህፍት አንድ ለአንድ እንዲደርሳቸው መደረጉን ፣ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በተዘጋጀበት አግባብም ተገቢውን እውቀት እንዲጨብጡ ጥረት መደረጉን ተናግረዋል።፡
ተማሪዎች በአግባቡ መዘጋጀት እንዲችሉና የሚገባቸውን እውቀት እንዲጨብጡ ለማድረግም ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት መሰጠቱንም ፣ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አመልክተዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር መምህራን ትርፍ ጊዜያቸውን ጭምር ተጠቅመው ተማሪዎችን ሲረዱ መቆታቸውን የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ወላጆችና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችም ተማሪዎችን ሲደግፉና ክትትል ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል።
ፈተናው በወረቅትና በበይነ መረብ እንደሚሰጥ የጠቆሙት ክረብርት ወ/ሮ አየለች በተለይ ፈተናው በበይነ መረብ መሰጠቱ ስርቆትና ኩረጃን በማስቀረት ረገድ ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም ተማሪዎች ፈተናውን በተረጋጋ ሁኑታ እንዲፈተኑና መልካም እድል እንዲገጥማቸው ተመኝተዋል፡፡
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ከዛሬ ጀምሮ በሚሰጠው ብሄራዊ ፈተና በአስተዳደሩ 280 ትምህርት ቤቶች 51 ሺ 259 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ አስታውቀዋል፡፡
የትምህርት ምዘናና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው በአገር አቀፍ ደረጃ ከ608 ሺ የሚበልጡ ተማሪዎች በወረቅትና በበይነ መረብ ፈተና እንደሚወሰዱ ጠቁመዋል፡፡
ክብርት ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ ፈተናውን በአዲስ አበባ አስጀምረዋል።፡
ክብርት የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ ከተማ እየተሰጠ የሚገኘውን ፈተና በአብርሆት ቤተ መጻህፍት ባስጀመሩበት ውቅት እንደገለጹት ለፈተናው ተገቢው የቅድመ ዝግጅት ስራ ተሰርቷል፡፡
ተማሪዎች አዲሱን ስርኣት ትምህርት መሰረት በማድረግ መጻህፍት አንድ ለአንድ እንዲደርሳቸው መደረጉን ፣ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በተዘጋጀበት አግባብም ተገቢውን እውቀት እንዲጨብጡ ጥረት መደረጉን ተናግረዋል።፡
ተማሪዎች በአግባቡ መዘጋጀት እንዲችሉና የሚገባቸውን እውቀት እንዲጨብጡ ለማድረግም ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት መሰጠቱንም ፣ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አመልክተዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር መምህራን ትርፍ ጊዜያቸውን ጭምር ተጠቅመው ተማሪዎችን ሲረዱ መቆታቸውን የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ወላጆችና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችም ተማሪዎችን ሲደግፉና ክትትል ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል።
ፈተናው በወረቅትና በበይነ መረብ እንደሚሰጥ የጠቆሙት ክረብርት ወ/ሮ አየለች በተለይ ፈተናው በበይነ መረብ መሰጠቱ ስርቆትና ኩረጃን በማስቀረት ረገድ ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም ተማሪዎች ፈተናውን በተረጋጋ ሁኑታ እንዲፈተኑና መልካም እድል እንዲገጥማቸው ተመኝተዋል፡፡
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ከዛሬ ጀምሮ በሚሰጠው ብሄራዊ ፈተና በአስተዳደሩ 280 ትምህርት ቤቶች 51 ሺ 259 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ አስታውቀዋል፡፡
የትምህርት ምዘናና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው በአገር አቀፍ ደረጃ ከ608 ሺ የሚበልጡ ተማሪዎች በወረቅትና በበይነ መረብ ፈተና እንደሚወሰዱ ጠቁመዋል፡፡
Jun 30, 2025 392
Recent News
Follow Us