News

National News

የትምህርት ሚኒስቴር እና የጣሊያን ከፍተኛ ትምህርትና ምርምር ሚኒስቴር በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ።

የስምምነቱን ሰነዱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የጣልያን ከፍተኛ ትምህርት እና ምርምር ሚኒስትር አና ማሪያ ፈርመውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በሁለቱ ሀገራት የተደረገው ስምምነት በትምህርቱ ዘርፍ የተጀመሩ ሥራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች እንዳሉ ገልጸው የሚደረገው ድጋፍ ፍትሃዊና ለታለመለት አላማ እንዲውል ማድረግ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ እንዲሆኑ እየተሰራ ያለውን ሥራ እና በትምህርቱ ዘርፍ ትብብር የሚሹ ጉዳዮችን ለሚኒስትሯ አብራርተውላቸዋል።
የጣሊያን የከፍተኛ ትምህርት እና ምርምር ሚኒስትር አና ማሪያ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ የጣሊያን አጋር መሆኗን አንስተው ሁለቱ ሀገራት በትምህርቱ ዘርፍ በላቀ ትብብር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
የተፈረመው መግባቢያ ስምምነት በጣሊያን እና በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል ቀጥተኛ ትብብር እንዲኖር የሚያበረታታ ነው ተብሏል።
ከዚህም በተጨማሪም በጣልያን መንግስት እና UNOPS አጋርነት በኢትዮጵያ ለሚገነቡ ሁለት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ መግባቢያ ስምምነትም ሁለቱ ሚኒስትሮች በተገኙበት ተፈርሟል።
ስምምነቱን በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ኦግስቲኖ ፖሌሲ እና የአፍሪካ ቀንድ ባለብዙ ሃገራት የዩኖፕስ (UNOPS) ቢሮ ዳይሬክተርና የአፍሪካ ህብረት ተወካይ ወ/ሮ ወርቅነሽ መኮንን ፈርመውታል።
የስምምነቱን ሰነዱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የጣልያን ከፍተኛ ትምህርት እና ምርምር ሚኒስትር አና ማሪያ ፈርመውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በሁለቱ ሀገራት የተደረገው ስምምነት በትምህርቱ ዘርፍ የተጀመሩ ሥራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች እንዳሉ ገልጸው የሚደረገው ድጋፍ ፍትሃዊና ለታለመለት አላማ እንዲውል ማድረግ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ እንዲሆኑ እየተሰራ ያለውን ሥራ እና በትምህርቱ ዘርፍ ትብብር የሚሹ ጉዳዮችን ለሚኒስትሯ አብራርተውላቸዋል።
የጣሊያን የከፍተኛ ትምህርት እና ምርምር ሚኒስትር አና ማሪያ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ የጣሊያን አጋር መሆኗን አንስተው ሁለቱ ሀገራት በትምህርቱ ዘርፍ በላቀ ትብብር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
የተፈረመው መግባቢያ ስምምነት በጣሊያን እና በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል ቀጥተኛ ትብብር እንዲኖር የሚያበረታታ ነው ተብሏል።
ከዚህም በተጨማሪም በጣልያን መንግስት እና UNOPS አጋርነት በኢትዮጵያ ለሚገነቡ ሁለት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ መግባቢያ ስምምነትም ሁለቱ ሚኒስትሮች በተገኙበት ተፈርሟል።
ስምምነቱን በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ኦግስቲኖ ፖሌሲ እና የአፍሪካ ቀንድ ባለብዙ ሃገራት የዩኖፕስ (UNOPS) ቢሮ ዳይሬክተርና የአፍሪካ ህብረት ተወካይ ወ/ሮ ወርቅነሽ መኮንን ፈርመውታል።
Jan 28, 2025 344
National News

የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ጥራትን ለማስጠበቅ በተዘጋጀው የጥራት ኦዲት መመሪያ እና ስታንዳርድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ።

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በውይይቱ መክፈቻ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት ቁልፍ መልእክት የትምህርት ስርዓቱ ፍትሃዊ፣ አካታች፣ ተደራሽነት ያለውና ችግር ፈቺ ለማድረግ በሚደረጉ ጥረቶች ውስጥ የባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ቀጣይነት ያለውና እየተሻሻለ የሚሄድ የውስጥ ጥራት አጠባበቅ ስርዓት የመዘርጋት፣ ስታንደርዶችን የማውጣትና ተግባራዊነታቸውን የማረጋገጥ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ሚንስትር ዴኤታው አያይዘው ገልጸዋል።
በዚህም ዜጎች የሀገሪቱን ልማትና ዕድገት ለማሳለጥ የሚያስችል ዕውቀት፤ ክህሎት እና አመለካከት ይዘው እንዲወጡና ከዘመኑ ጋር የሚሄድ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ኦዲት መመሪያ እና ስታንዳርዶች የተዘጋጁ መሆኑ ተገልጿል።
የትምህርት ተቋማቱ በቀጣይ መመሪያው ከጸደቀ በኋላ በአዲሱ የስልጠና ጥራት ኦዲት መመሪያ እና ስታንዳርድ መሠረት የሚመዘኑ መሆኑ ተጠቁሟል
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በውይይቱ መክፈቻ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት ቁልፍ መልእክት የትምህርት ስርዓቱ ፍትሃዊ፣ አካታች፣ ተደራሽነት ያለውና ችግር ፈቺ ለማድረግ በሚደረጉ ጥረቶች ውስጥ የባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ቀጣይነት ያለውና እየተሻሻለ የሚሄድ የውስጥ ጥራት አጠባበቅ ስርዓት የመዘርጋት፣ ስታንደርዶችን የማውጣትና ተግባራዊነታቸውን የማረጋገጥ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ሚንስትር ዴኤታው አያይዘው ገልጸዋል።
በዚህም ዜጎች የሀገሪቱን ልማትና ዕድገት ለማሳለጥ የሚያስችል ዕውቀት፤ ክህሎት እና አመለካከት ይዘው እንዲወጡና ከዘመኑ ጋር የሚሄድ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ኦዲት መመሪያ እና ስታንዳርዶች የተዘጋጁ መሆኑ ተገልጿል።
የትምህርት ተቋማቱ በቀጣይ መመሪያው ከጸደቀ በኋላ በአዲሱ የስልጠና ጥራት ኦዲት መመሪያ እና ስታንዳርድ መሠረት የሚመዘኑ መሆኑ ተጠቁሟል
Jan 26, 2025 285
National News

ስፖርትና እውቀትን በማቀናጀት በትምህርት ጥራት ላይ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ።

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ተከፍቷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፌስቲቫሉን ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር ስፖርትና እውቀትን ከትምህርት ጥራት ስራዎች ጋር በማስተሳሰር የአገርን እድገት ከፍ ማድረግ ይገባል፡፡
የአእምሮ እድገትና የአካል እድገት የተሳሰሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ተወዳዳሪዎች በቆይታቸው ሰላምን፤ ወዳጅነትና አብሮነትን በማስቀደም የስፖርት ፌስቲቫሎችን ማካሄድ እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል።
ከሚቀጥለው የትምህት ዘመን ጀምሮ ዩኒቨርስቲዎችን ጨምሮ በአገር ውስጥ ያሉ ትምህርት ቤቶች በሙሉ አዲስ የሊግ ወድድሮች እንደሚያካሄዱም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ከመጀመሪያ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ያሉ ትምህርት ቤቶች በሊግ ተደራጅተው ከወዲሁ ውድድሮችን በማካሄድ ላይ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ በበኩላቸው የዩቨርስቲዎች ስፖርት ፌስቲቫል በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ስፖርት ማዘውተሪያዎች እንዲስፋፉ ፣ በዩኒቨርስቲዎችና በተማሪዎች መካከል መልካም ግንኙነት እንዲፈጠር፣ የስፖርት ተሳትፎ እንዲጎለብትና ምቹ መማማር ማስተማር ከባቢ እንዲፈጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ስፖርት ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አባይ በላይሁን በበኩላቸው ውድድሩ በኮቪድና በተለያዩ ምክንያቶች ለዘጠኝ አመታት ተቋርጦ የቆየውን ውድድር ትምህርት ሚኒስቴር ዩኒቨርስቲዎች ተቀራራቢ ካላንደር እንዲኖራቸው በማድረጉ እውን ሊሆን መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡
የውድድሩ አዘጋጅ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ደረጀ እንግዳ በዚሁ ጊዜ ሲናገሩ ስፖርት ለአንድነትና ለእድገት በሚል መሪ ቃል የሚካሄደውን ይህን የስፖርት ፌስቲቫል ቀጣይነት ለማረጋገጥ ዩኒቨርስቲው በአጭር ጊዜ ወስጥ ውድድሩን ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ከጥር 17 – 27/ 2017 ዓ.ም በሚካሄደው በዚህ ውድድር በአምስት ስፖርት አይነቶች ከ49 ዩኒቨርስቲዎች የተውጣቱ 2500 ስፖርተኞች እንደሚሳተፉ ታውቋል።
የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ተከፍቷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፌስቲቫሉን ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር ስፖርትና እውቀትን ከትምህርት ጥራት ስራዎች ጋር በማስተሳሰር የአገርን እድገት ከፍ ማድረግ ይገባል፡፡
የአእምሮ እድገትና የአካል እድገት የተሳሰሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ተወዳዳሪዎች በቆይታቸው ሰላምን፤ ወዳጅነትና አብሮነትን በማስቀደም የስፖርት ፌስቲቫሎችን ማካሄድ እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል።
ከሚቀጥለው የትምህት ዘመን ጀምሮ ዩኒቨርስቲዎችን ጨምሮ በአገር ውስጥ ያሉ ትምህርት ቤቶች በሙሉ አዲስ የሊግ ወድድሮች እንደሚያካሄዱም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ከመጀመሪያ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ያሉ ትምህርት ቤቶች በሊግ ተደራጅተው ከወዲሁ ውድድሮችን በማካሄድ ላይ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ በበኩላቸው የዩቨርስቲዎች ስፖርት ፌስቲቫል በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ስፖርት ማዘውተሪያዎች እንዲስፋፉ ፣ በዩኒቨርስቲዎችና በተማሪዎች መካከል መልካም ግንኙነት እንዲፈጠር፣ የስፖርት ተሳትፎ እንዲጎለብትና ምቹ መማማር ማስተማር ከባቢ እንዲፈጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ስፖርት ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አባይ በላይሁን በበኩላቸው ውድድሩ በኮቪድና በተለያዩ ምክንያቶች ለዘጠኝ አመታት ተቋርጦ የቆየውን ውድድር ትምህርት ሚኒስቴር ዩኒቨርስቲዎች ተቀራራቢ ካላንደር እንዲኖራቸው በማድረጉ እውን ሊሆን መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡
የውድድሩ አዘጋጅ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ደረጀ እንግዳ በዚሁ ጊዜ ሲናገሩ ስፖርት ለአንድነትና ለእድገት በሚል መሪ ቃል የሚካሄደውን ይህን የስፖርት ፌስቲቫል ቀጣይነት ለማረጋገጥ ዩኒቨርስቲው በአጭር ጊዜ ወስጥ ውድድሩን ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ከጥር 17 – 27/ 2017 ዓ.ም በሚካሄደው በዚህ ውድድር በአምስት ስፖርት አይነቶች ከ49 ዩኒቨርስቲዎች የተውጣቱ 2500 ስፖርተኞች እንደሚሳተፉ ታውቋል።
Jan 26, 2025 294
National News

በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ከተማ ለሚገነባው ልዩ አዳሪ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመሰረት ድንጋይ በዛሬው ዕለት ተቀምጧል፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ደ/ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ከተማ ለሚገነባው ልዩ አደሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በማስጀመር የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወቅቱ እንዳሉት ብቁ፣ ተወዳዳሪና ለወደፊት ለሀገሪቱ ጠንካራ መሪ ለማውጣት ግብዓት የተሟላላቸው አዳሪ ትምህርት ቤቶችን መገንባት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚቻለው ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ማድረስ ሲቻል ነው ያሉት ሚኒስትሩ በገጠርም ሆነ በከተማ ሁሉም ዜጋ ጥሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኝም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የዚህ ትምህርት ቤት ግንባታ በዚህ አመት ተጠናቆ ከመላው ሀገሪቱ ከ8ኛ ክፍል በጣም ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ተመርጠው የሚማሩባት እንደሆነም ገልፀዋል።
በዚህም የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ለልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ ግንባታ ቦታ በማዘጋጀትና የግንባታ ወጪን መሸፈን ላደረገው ድጋፍም ሚኒስትሩ ምስጋና አቅርበዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ከሌሎቹ ለየት የሚያደርገው ከኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን ከመላው ኢትዮጵያ ብቃት ያላቸው ተማሪዎች ተመርጠው የሚማሩበት መሆኑ ነው ብለዋል።
በ1.27 ቢሊየን ብር ወጪ የሚገነባው ይህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ሙሉ ወጪ በክልሉ መንግስት እንደሚሸፈን ገልፀው ይህም ክልሉ ለትምህርት የሰጠውን ትኩረት ያሳያል ብለዋል።
የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ ግንባታ በዚህ ዓመት ተጠናቅቆ በመስከረም 2018 ዓ.ም የመጀመሪያዎቹን 250 ተማሪዎች ተቀብሎ የማስተማር ሥራውን እንደሚጀመር ጠቁመዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርታቸው ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እያስገነባ እንደሚገኝም በመድረኩ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅም ለመጀመሪያ ጊዜ 1500 የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር ይጀምራሉ ተብሏል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ደ/ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ከተማ ለሚገነባው ልዩ አደሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በማስጀመር የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወቅቱ እንዳሉት ብቁ፣ ተወዳዳሪና ለወደፊት ለሀገሪቱ ጠንካራ መሪ ለማውጣት ግብዓት የተሟላላቸው አዳሪ ትምህርት ቤቶችን መገንባት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚቻለው ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ማድረስ ሲቻል ነው ያሉት ሚኒስትሩ በገጠርም ሆነ በከተማ ሁሉም ዜጋ ጥሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኝም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የዚህ ትምህርት ቤት ግንባታ በዚህ አመት ተጠናቆ ከመላው ሀገሪቱ ከ8ኛ ክፍል በጣም ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ተመርጠው የሚማሩባት እንደሆነም ገልፀዋል።
በዚህም የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ለልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ ግንባታ ቦታ በማዘጋጀትና የግንባታ ወጪን መሸፈን ላደረገው ድጋፍም ሚኒስትሩ ምስጋና አቅርበዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ከሌሎቹ ለየት የሚያደርገው ከኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን ከመላው ኢትዮጵያ ብቃት ያላቸው ተማሪዎች ተመርጠው የሚማሩበት መሆኑ ነው ብለዋል።
በ1.27 ቢሊየን ብር ወጪ የሚገነባው ይህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ሙሉ ወጪ በክልሉ መንግስት እንደሚሸፈን ገልፀው ይህም ክልሉ ለትምህርት የሰጠውን ትኩረት ያሳያል ብለዋል።
የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ ግንባታ በዚህ ዓመት ተጠናቅቆ በመስከረም 2018 ዓ.ም የመጀመሪያዎቹን 250 ተማሪዎች ተቀብሎ የማስተማር ሥራውን እንደሚጀመር ጠቁመዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርታቸው ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እያስገነባ እንደሚገኝም በመድረኩ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅም ለመጀመሪያ ጊዜ 1500 የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር ይጀምራሉ ተብሏል።
Jan 23, 2025 251
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ጋር ተወያዩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሃንፊልድ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸው የትምህርት ሚኒስትሩ በትምህርት ሥርዓቱ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ በማድረግ ተወዳዳሪና ብቁ ትውልድ ለመፍጠር እየተተገበሩ ስላሉ የሪፎርም ሥራዎች እና ድጋፍ የሚሹ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አብራርተዋል።
በዚህም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትምህርት ዘርፉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን፣ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ የትምህርት ተቋማትን መልሶ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራሳቸውን የሚያስተዳድሩ፣ ነጻ ሃሳብ የሚራመድባቸው፣ ትክክለኛ የማስተማሪያና የምርምር ተቋማት እንዲሆኑ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን እንዲደግፉም ጠይቀዋል።
በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሃንፊልድ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ጀርመን ለረጅም ጊዜ የቆየ መልካም ግንኙነት እንደነበራቸው ገልጽው ይህንን አጠናክረው መቀጠል እንደሚፈልጉም ተናግረዋል።
በተለይም በክቡር ሚኒስትሩ የቀረቡትን በኢትዮጵያ የጀርመን ትምህርት ቤት ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች የነጻ የትምህርት እድል የሚያገኙበትን፣ በሰው ሰራሽና ተፈጥሮ አደጋ የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ በመገንባትና በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ስራዎችን በመደግፍ ረገድ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩም አብራርተዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሃንፊልድ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸው የትምህርት ሚኒስትሩ በትምህርት ሥርዓቱ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ በማድረግ ተወዳዳሪና ብቁ ትውልድ ለመፍጠር እየተተገበሩ ስላሉ የሪፎርም ሥራዎች እና ድጋፍ የሚሹ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አብራርተዋል።
በዚህም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትምህርት ዘርፉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን፣ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ የትምህርት ተቋማትን መልሶ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራሳቸውን የሚያስተዳድሩ፣ ነጻ ሃሳብ የሚራመድባቸው፣ ትክክለኛ የማስተማሪያና የምርምር ተቋማት እንዲሆኑ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን እንዲደግፉም ጠይቀዋል።
በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሃንፊልድ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ጀርመን ለረጅም ጊዜ የቆየ መልካም ግንኙነት እንደነበራቸው ገልጽው ይህንን አጠናክረው መቀጠል እንደሚፈልጉም ተናግረዋል።
በተለይም በክቡር ሚኒስትሩ የቀረቡትን በኢትዮጵያ የጀርመን ትምህርት ቤት ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች የነጻ የትምህርት እድል የሚያገኙበትን፣ በሰው ሰራሽና ተፈጥሮ አደጋ የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ በመገንባትና በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ስራዎችን በመደግፍ ረገድ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩም አብራርተዋል።
Jan 17, 2025 448
National News

በ2017 ዓ.ም አጋማሽ የሚሰጠውን የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተናን ዳግም ለመውሰድ ፍላጎት ያላችሁ አመልካቾች

 ይህንን ሊንክ https://exam.ethernet.edu.et በመጫን መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

 ይህንን ሊንክ https://exam.ethernet.edu.et በመጫን መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

Jan 16, 2025 1K
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባስደርን በጽ/ ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ከሆኑት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገር ጋር ተወያይተዋል።
በዚሁ ወቅት ትምህርት ሚኒስቴር ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በአጠቃላይና በከፍተኛ ትምህርት ዘርፎች እየተተገበሩ ያሉ የለውጥ እርምጃዎችንና የትኩረት አቅጣጫዎችን ለአምባሰደሯ አብራርተዋል።
በተለይም ጥራት ያለው ፍትሃዊ ትምህርት ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የቅድመ ልጅነት ትምህርት፣ የመምህራንን የማስተማር አቅም ማሳደግ፣ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ማሻሻል እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ ማድረግ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።
አክለውም በትምህርት ዘርፉ ድጋፍ የሚያደርጉ አጋር አካላት የቅድሚያ ትኩረት የተሰጣቸውና የተማሪዎችን እኩል የመማር መብት የሚያረጋግጡ ጉዳዮች ላይ መሆን እንዳለበት ገልጸው ለዚህም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመወያየት በጋራ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገርን በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥቶ እየስራቸው ላሉ ስራዎች አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገላጸዋል።
ሁለቱ አካላት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት እየተወሰዱ ያሉ የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው በሚቀጥሉበት ጉዳይ ላይም ሰፊ ውይይት አድረገዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ከሆኑት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገር ጋር ተወያይተዋል።
በዚሁ ወቅት ትምህርት ሚኒስቴር ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በአጠቃላይና በከፍተኛ ትምህርት ዘርፎች እየተተገበሩ ያሉ የለውጥ እርምጃዎችንና የትኩረት አቅጣጫዎችን ለአምባሰደሯ አብራርተዋል።
በተለይም ጥራት ያለው ፍትሃዊ ትምህርት ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የቅድመ ልጅነት ትምህርት፣ የመምህራንን የማስተማር አቅም ማሳደግ፣ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ማሻሻል እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ ማድረግ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።
አክለውም በትምህርት ዘርፉ ድጋፍ የሚያደርጉ አጋር አካላት የቅድሚያ ትኩረት የተሰጣቸውና የተማሪዎችን እኩል የመማር መብት የሚያረጋግጡ ጉዳዮች ላይ መሆን እንዳለበት ገልጸው ለዚህም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመወያየት በጋራ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገርን በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥቶ እየስራቸው ላሉ ስራዎች አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገላጸዋል።
ሁለቱ አካላት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት እየተወሰዱ ያሉ የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው በሚቀጥሉበት ጉዳይ ላይም ሰፊ ውይይት አድረገዋል።
Jan 14, 2025 240
National News

ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ የልዩ ትምህርት ፍላጎት ያላቸው ዜጎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡና ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የሁሉንም ባለድርሻዎችና አጋሮች ድጋፍና ትብብር እንደሚፈልግ ተገለጸ።

በልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ላይ ከአካል ጉዳተኞች ማህበራት ጋር ምክክር ተደርጓል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የምክክር መድረኩን ሲከፍቱ እንደገለጹት እድሜያቸው ለትምህርት የደረሰና ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ሁሉም ልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸው ህጻናት ወጣቶችና ጎልማሶች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡና ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የሁሉንም ተሳትፎ የሚጠይቅ ተግባር ነው።
ልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸውን ዜጎች የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሻሻልና አካቶ ትምህርትን ለመተግበር በስራው ዙሪያ ንቁ ተሳትፎ ካላቸው የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና አጋሮች ጋር በትብብር መስራቱ ለስራው ውጤታማነት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል፡፡
በ2015 ዓ.ም በወጣው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ልዩ ተሰጥዎና ተውህቦ ያላቸው፣ የአካል ጉዳትና ልዩ የመማር ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች የሚያስተናግድ ስርአተ ትምህርት ተዘጋጅቶ ስራ ላይ እንዲውል አቅጣጫ መቀመጡንም ሚኒስትር ዴኤታዋ አመልክተዋል፡።
ልዩ ፍላጎት ያላቸው ሁሉም ህፃናት ወጣቶችና ጎልማሶች የትምህርት ጥራትና ተገቢነት ያለው ፍትሃዊ የሆነ ትምህርትና ስልጠና ተደራሽ በማድረግ በአገራቸው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ውስጥ ሙሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ የሚያስችል የአካቶ ትምህርት ስርዓትን ለመገንባት ስትራቴጂ መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል፡፡
የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራትና መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዩሀንስ ወጋሶ በበኩላቸው ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግና በትምህርት ቤት ውስጥ የሚያገኙትን ትምህርት ለማሻሻል በተዘጋጀው የልዩ ትምህርት ስትራቴጂ የተቀመጡ ዋና ዋና ምሶሶዎችን በመተግበር የልዩ ፍላጎት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡።
የአርብቶ አደርና የልዩ ፍላጎት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ መሠረት በቀለ በዚሁ ወቅት ባቀረቡት ጽሁፍ ወደ ትምህርት ቤት ያልመጡና ትምህርት ቤቶችም ምቹ ባለመሆናቸው ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ በርካታ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ተማሪዎች መኖራቸውን ጠቁመው የድጋፍ መስጫ ማዕካትን በማቋቋምና የመምህራንን ክህሎት በማሳደግ የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡
የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው ማህበራት ህብረተሰቡን ማንቃትና በሚሰሩ ስራዎች ላይም የሚያስፈልጉ ምክረ ሀሳቦችን በመስጠት የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሳደግ በጋራ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል።
በልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ላይ ከአካል ጉዳተኞች ማህበራት ጋር ምክክር ተደርጓል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የምክክር መድረኩን ሲከፍቱ እንደገለጹት እድሜያቸው ለትምህርት የደረሰና ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ሁሉም ልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸው ህጻናት ወጣቶችና ጎልማሶች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡና ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የሁሉንም ተሳትፎ የሚጠይቅ ተግባር ነው።
ልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸውን ዜጎች የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሻሻልና አካቶ ትምህርትን ለመተግበር በስራው ዙሪያ ንቁ ተሳትፎ ካላቸው የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና አጋሮች ጋር በትብብር መስራቱ ለስራው ውጤታማነት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል፡፡
በ2015 ዓ.ም በወጣው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ልዩ ተሰጥዎና ተውህቦ ያላቸው፣ የአካል ጉዳትና ልዩ የመማር ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች የሚያስተናግድ ስርአተ ትምህርት ተዘጋጅቶ ስራ ላይ እንዲውል አቅጣጫ መቀመጡንም ሚኒስትር ዴኤታዋ አመልክተዋል፡።
ልዩ ፍላጎት ያላቸው ሁሉም ህፃናት ወጣቶችና ጎልማሶች የትምህርት ጥራትና ተገቢነት ያለው ፍትሃዊ የሆነ ትምህርትና ስልጠና ተደራሽ በማድረግ በአገራቸው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ውስጥ ሙሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ የሚያስችል የአካቶ ትምህርት ስርዓትን ለመገንባት ስትራቴጂ መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል፡፡
የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራትና መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዩሀንስ ወጋሶ በበኩላቸው ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግና በትምህርት ቤት ውስጥ የሚያገኙትን ትምህርት ለማሻሻል በተዘጋጀው የልዩ ትምህርት ስትራቴጂ የተቀመጡ ዋና ዋና ምሶሶዎችን በመተግበር የልዩ ፍላጎት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡።
የአርብቶ አደርና የልዩ ፍላጎት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ መሠረት በቀለ በዚሁ ወቅት ባቀረቡት ጽሁፍ ወደ ትምህርት ቤት ያልመጡና ትምህርት ቤቶችም ምቹ ባለመሆናቸው ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ በርካታ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ተማሪዎች መኖራቸውን ጠቁመው የድጋፍ መስጫ ማዕካትን በማቋቋምና የመምህራንን ክህሎት በማሳደግ የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡
የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው ማህበራት ህብረተሰቡን ማንቃትና በሚሰሩ ስራዎች ላይም የሚያስፈልጉ ምክረ ሀሳቦችን በመስጠት የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሳደግ በጋራ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል።
Jan 05, 2025 283
National News

በማዕከላዊ ቀጠና ስር የተመደበው የኦሮምያ ብሄራዊ ክልል የተማሪዎች የስፖርት ሊግን አስጀመረ።

በኦሮምያ ክልል የትምህርት ቤቶች የስፖርት ሊግ ውድድር በአዳማ ከተማ በስምንት የመንግስት አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች መካሄድ ጀምሯል።
ስፖርትዊ ውድድሩ የክልሉና የአዳማ ከተማ አስተዳደር አመራሮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል።
ውድድሮቹ የተጀመሩት በእግር ኳስ፣ በቮሊቦል እና በአትሌቲክስ ስፖርት አይነቶች ሲሆን በሁሉም ውድድሮች በርካታ ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
የስፖርት ውድድሩ ተማሪዎች ያላቸውን መልካም ግንኙነት ከማጠናከር ባለፈ በአካልና በአእምሮ እንዲሁም ሁለንተናዊ ስብዕና የተላበሱ ቀልጣፋ ዜጋ እንዲሆኑ እንደሚያደርጋቸው በማስጀመሪያ መድረኩ ላይ ተገልጿል።
በተጨማሪም ስፖርታዊ ውድድሩ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማሳለጥ የጤናና የሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ትልቅ ሚናና ድርሻ እንዳለው በማመን ወደ ስራ የተገባ መሆኑም ተገልጿል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የተማሪዎች የስፖርት ውድድር በተለያዩ የምድብ ቀጠናዎች እየተካሄደ ይገኛል።
በኦሮምያ ክልል የትምህርት ቤቶች የስፖርት ሊግ ውድድር በአዳማ ከተማ በስምንት የመንግስት አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች መካሄድ ጀምሯል።
ስፖርትዊ ውድድሩ የክልሉና የአዳማ ከተማ አስተዳደር አመራሮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል።
ውድድሮቹ የተጀመሩት በእግር ኳስ፣ በቮሊቦል እና በአትሌቲክስ ስፖርት አይነቶች ሲሆን በሁሉም ውድድሮች በርካታ ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
የስፖርት ውድድሩ ተማሪዎች ያላቸውን መልካም ግንኙነት ከማጠናከር ባለፈ በአካልና በአእምሮ እንዲሁም ሁለንተናዊ ስብዕና የተላበሱ ቀልጣፋ ዜጋ እንዲሆኑ እንደሚያደርጋቸው በማስጀመሪያ መድረኩ ላይ ተገልጿል።
በተጨማሪም ስፖርታዊ ውድድሩ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማሳለጥ የጤናና የሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ትልቅ ሚናና ድርሻ እንዳለው በማመን ወደ ስራ የተገባ መሆኑም ተገልጿል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የተማሪዎች የስፖርት ውድድር በተለያዩ የምድብ ቀጠናዎች እየተካሄደ ይገኛል።
Dec 25, 2024 294
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአገሪቱን እድገትና የህዝቡን ህይወት ለማሻሻል ቅድሚያ ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስገነዘቡ።

ትምህርት ሚኒስቴር ከአርባ ሰባት (47) የመንግስተት ዩኒቨርስቲዎች ጋር በ2017 የሚተገበር ቁልፍ የአፈጻጸመም ውል ተፈራርሟል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በስምምነቱ ወቅተት እንደገለጹት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሯቸው ምርምሮችና የሚያፈሯቸው ዜጎች አገር የሚለውጡና ከዓለም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል።
ዩኒቨርስቲዎች ራሳቸውን ወደ ራስገዝነት እያሳደጉ እድገታቸውንና ቀጣይነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የተፈረመው ውል ሃላፊነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የትምህርትና የምርምር ጥራትን በማስጠበቅ ብቃትና ጥራት ያለው ዜጋ ማፍራት ግዴታ መሆኑን አውቀው በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
በቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ ስምምነቱ መሠረት ውጤት የሚያስመዘግቡ ተቋማት በበጀት ጭምር የበለጠ የሚደገፉበት፣ ወደ ኋላ የሚቀሩና ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚያስመዘግቡት ደግሞ ተጠያቂ የሚሆኑበት እንደሆነ ጠቁመዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የቁልፍ ስራዎች አፈጻጸም ውሉ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያዎች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እንደሚያስችል ገልጸዋል።
ስምምነቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ስርዓት እንዲኖርና ዩኒቨርስቲዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚያደርግም ጠቅሰዋል።
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርተ ተቋማቱ በገቡት ስምምነት መሠረት ስራዎቻቸውን በየደረጃው በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ቀጣይነት ያለው ውጤት ለማስመዝገብ መረባረብ እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትሩን በመወከል የከፍተኛ ትምህርቶ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አት ኮራ ጡሹኔ ዩኒቨርስቲዎቹን በመወከል ደግሞ የየዩኒቨርስቲዎቹ ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚዳንቶች ፈርመዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከአርባ ሰባት (47) የመንግስተት ዩኒቨርስቲዎች ጋር በ2017 የሚተገበር ቁልፍ የአፈጻጸመም ውል ተፈራርሟል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በስምምነቱ ወቅተት እንደገለጹት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሯቸው ምርምሮችና የሚያፈሯቸው ዜጎች አገር የሚለውጡና ከዓለም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል።
ዩኒቨርስቲዎች ራሳቸውን ወደ ራስገዝነት እያሳደጉ እድገታቸውንና ቀጣይነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የተፈረመው ውል ሃላፊነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የትምህርትና የምርምር ጥራትን በማስጠበቅ ብቃትና ጥራት ያለው ዜጋ ማፍራት ግዴታ መሆኑን አውቀው በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
በቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ ስምምነቱ መሠረት ውጤት የሚያስመዘግቡ ተቋማት በበጀት ጭምር የበለጠ የሚደገፉበት፣ ወደ ኋላ የሚቀሩና ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚያስመዘግቡት ደግሞ ተጠያቂ የሚሆኑበት እንደሆነ ጠቁመዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የቁልፍ ስራዎች አፈጻጸም ውሉ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያዎች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እንደሚያስችል ገልጸዋል።
ስምምነቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ስርዓት እንዲኖርና ዩኒቨርስቲዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚያደርግም ጠቅሰዋል።
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርተ ተቋማቱ በገቡት ስምምነት መሠረት ስራዎቻቸውን በየደረጃው በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ቀጣይነት ያለው ውጤት ለማስመዝገብ መረባረብ እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትሩን በመወከል የከፍተኛ ትምህርቶ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አት ኮራ ጡሹኔ ዩኒቨርስቲዎቹን በመወከል ደግሞ የየዩኒቨርስቲዎቹ ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚዳንቶች ፈርመዋል።
Dec 25, 2024 385
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ስራ በውጤታማነት ለመፈጸም የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።

በትምህርት ሚኒስቴርና በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል ነገ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም የሚፈረመው ስምምነት ተቋማት ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን በማፍራት ሂደት ውስጥ ተጠያቂነትን ከማስፈን ባለፈ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒሰትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች / Key Performance Indicators / 47 ዩኒቨርስቲዎች ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ድርድር ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት ከተያዘው 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ዩኒቨርስቲዎች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪና ለስራ ገበያው የሚመጥን ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን ማፍራት እንዲችሉ ከተያዘው 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ስራን በውጤት መምራት ወደሚያስችል ስርዓት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ተቋማቱ ስራን በውጤት መምራት ወደሚያችል ስርዓት ማስገባት በሙያዊና ክህሎታዊ ስራዎች እንዲሁም በልህቀት ላይ በማተኮር የአገሪቱን ችግሮች መፍታት የሚችሉ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚን የማልማት ስራ ላይ የበኩላቸውን ወሳኝ ሚና እንዲጫወቱ እንደሚያስችላቸው ክቡር አቶ ኮራ ገልጸዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፈነ አመራር እንዲከተሉ ፣ አገሪቱ ለምታወጣው ሀብት ተመጣጣኝ ውጤት እንዲያስገኙ የአፈጻጸም አቅማቸው እንዲገመገምና ለስኬቱም እውቅና እና ሽልማት እንዲያገኙ እንደሚያግዝም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡
የጅጅጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር በሽር አብዱላሂ በዚሁ ጊዜ ሲናገሩ ስምምነቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስራዎችን ከስር ከመሰረታቸው በአግባቡ በመያዝ ከሚፈለገው ግብ ላይ ለመድረስና የተጠያቂነትና ውጤታማ የሀብት አጠቃቀም ስርዓት እንዲኖር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ብርሃነ መስቀል ጠና በበኩላቸው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ በትምህርት ባለሙያዎችና በመምህራን ትምህርት ላይ አተኩሮ የሚሰራ ተቋም እንደመሆኑ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ድርድርና ስምምነት የተደረገባቸው ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች ስራን ቆጥሮ በመረከብ በውጤታማነት ለመፈጸም እንደሚያችል ተናግረዋል፡፡
የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጴጥሮስ ወ/ ጊዮርጊስ ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎች ዩኒቨርስቲዎች ወዴት እንደሚሄዱና የት ቦታ ለመድረስ ማቀድ እንዳለባቸው የሚያስገድድ ውል መሆኑን ጠቁመው ከትምህርት ተቋማት ውጪ የሚገኙ ሌሎች ተቋማትም ቢተገብሩት ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው አስረድተዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ስራን በውጤት መምራት ወደሚያችል ስርዓት ለማስገባት ሚያስችለው / KPI / ስምምነት 47ቱም የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶችና የቦርድ ሰብሳቢዎች ከትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር በነገው እለት በሚኖር ስነ ስርዓት በይፋ ይፈራረማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴርና በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል ነገ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም የሚፈረመው ስምምነት ተቋማት ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን በማፍራት ሂደት ውስጥ ተጠያቂነትን ከማስፈን ባለፈ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒሰትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች / Key Performance Indicators / 47 ዩኒቨርስቲዎች ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ድርድር ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት ከተያዘው 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ዩኒቨርስቲዎች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪና ለስራ ገበያው የሚመጥን ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን ማፍራት እንዲችሉ ከተያዘው 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ስራን በውጤት መምራት ወደሚያስችል ስርዓት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ተቋማቱ ስራን በውጤት መምራት ወደሚያችል ስርዓት ማስገባት በሙያዊና ክህሎታዊ ስራዎች እንዲሁም በልህቀት ላይ በማተኮር የአገሪቱን ችግሮች መፍታት የሚችሉ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚን የማልማት ስራ ላይ የበኩላቸውን ወሳኝ ሚና እንዲጫወቱ እንደሚያስችላቸው ክቡር አቶ ኮራ ገልጸዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፈነ አመራር እንዲከተሉ ፣ አገሪቱ ለምታወጣው ሀብት ተመጣጣኝ ውጤት እንዲያስገኙ የአፈጻጸም አቅማቸው እንዲገመገምና ለስኬቱም እውቅና እና ሽልማት እንዲያገኙ እንደሚያግዝም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡
የጅጅጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር በሽር አብዱላሂ በዚሁ ጊዜ ሲናገሩ ስምምነቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስራዎችን ከስር ከመሰረታቸው በአግባቡ በመያዝ ከሚፈለገው ግብ ላይ ለመድረስና የተጠያቂነትና ውጤታማ የሀብት አጠቃቀም ስርዓት እንዲኖር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ብርሃነ መስቀል ጠና በበኩላቸው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ በትምህርት ባለሙያዎችና በመምህራን ትምህርት ላይ አተኩሮ የሚሰራ ተቋም እንደመሆኑ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ድርድርና ስምምነት የተደረገባቸው ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች ስራን ቆጥሮ በመረከብ በውጤታማነት ለመፈጸም እንደሚያችል ተናግረዋል፡፡
የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጴጥሮስ ወ/ ጊዮርጊስ ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎች ዩኒቨርስቲዎች ወዴት እንደሚሄዱና የት ቦታ ለመድረስ ማቀድ እንዳለባቸው የሚያስገድድ ውል መሆኑን ጠቁመው ከትምህርት ተቋማት ውጪ የሚገኙ ሌሎች ተቋማትም ቢተገብሩት ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው አስረድተዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ስራን በውጤት መምራት ወደሚያችል ስርዓት ለማስገባት ሚያስችለው / KPI / ስምምነት 47ቱም የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶችና የቦርድ ሰብሳቢዎች ከትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር በነገው እለት በሚኖር ስነ ስርዓት በይፋ ይፈራረማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
Dec 24, 2024 285
National News

የት/ቤቶች ስፖርት ውድድር ለሀገራዊ ስፖርት ውጤታማነት የላቀ ሚና እንዳለው ተጠቆመ።

የ2017 የት/ቤቶች የስፖርት ውድድር ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱ ወቅት በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት መሰረተ ልማትና አገልግሎት ዴስክ ሃላፊ አቶ ታየ ግርማ እንደገለጹት የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድርን ማጠናከር ሳይቻል ሀገራዊ የስፖርት ውጤት መጠበቅ አይቻልም።
በተለያዩ ምክንያቶች ተቋርጦ የነበረው የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር በያዝነው የትምህርት ዘመን በዘጠኝ ቀጠናዎች ተደራጅቶ እየተከናወነ መሆኑን ሃላፊው ገልጸዋል።
በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የውድድር ስፖርቶች ክትትልና ድጋፍ ዴስክ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ዳርጌ የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር የተፈጠረውን ሀገራዊ የስፖርታዊ ውጤቶች መቀዛቀዝ ክፍተት ለመሙላት ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
ሚኒስቴሩ ለት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድሮች ትኩረት በመስጠት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በመፈራረም ወደ ስራ የተገባ መሆኑን ጠቁመው ይሄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር በት/ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ቦጋለ በበኩላቸው ስፖርቱ በማህበረሰቡ ድጋፍ እንዲያገኝ ሁላችንም በአገኘነው አጋጣሚ ሁሉ የማስተዋወቅ ስራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።
በዘጠኙም ቀጠናዎች የተደለደሉ ሁሉም ክልሎች የአፈጻጸም ሪፖርት አቅርበው ውይይት የተደረገ ሲሆን ከጥቂት ቀጠናዎች በስተቀር የስፖርት ሊጉን ስኬታማ ለማድረግ የአመራር ሚና በሚፈለገው ልክ ባለመሆኑ ይህ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቁሟል።
የ2017 የት/ቤቶች የስፖርት ውድድር ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱ ወቅት በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት መሰረተ ልማትና አገልግሎት ዴስክ ሃላፊ አቶ ታየ ግርማ እንደገለጹት የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድርን ማጠናከር ሳይቻል ሀገራዊ የስፖርት ውጤት መጠበቅ አይቻልም።
በተለያዩ ምክንያቶች ተቋርጦ የነበረው የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር በያዝነው የትምህርት ዘመን በዘጠኝ ቀጠናዎች ተደራጅቶ እየተከናወነ መሆኑን ሃላፊው ገልጸዋል።
በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የውድድር ስፖርቶች ክትትልና ድጋፍ ዴስክ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ዳርጌ የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር የተፈጠረውን ሀገራዊ የስፖርታዊ ውጤቶች መቀዛቀዝ ክፍተት ለመሙላት ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
ሚኒስቴሩ ለት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድሮች ትኩረት በመስጠት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በመፈራረም ወደ ስራ የተገባ መሆኑን ጠቁመው ይሄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር በት/ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ቦጋለ በበኩላቸው ስፖርቱ በማህበረሰቡ ድጋፍ እንዲያገኝ ሁላችንም በአገኘነው አጋጣሚ ሁሉ የማስተዋወቅ ስራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።
በዘጠኙም ቀጠናዎች የተደለደሉ ሁሉም ክልሎች የአፈጻጸም ሪፖርት አቅርበው ውይይት የተደረገ ሲሆን ከጥቂት ቀጠናዎች በስተቀር የስፖርት ሊጉን ስኬታማ ለማድረግ የአመራር ሚና በሚፈለገው ልክ ባለመሆኑ ይህ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቁሟል።
Dec 23, 2024 229
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕፌሰር ብርሃኑ ነጋ በደቡብ ሱዳን መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ከተመራ ልዑካን ቡድን ጋር ተወያዩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ትምህርት ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ገብሬላ ቻንግሰን ቻንግ የተመራ ልዑክን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ዜጎች እየሰጠች ባለችው የትምህርት እድልና ባጋጠሙ ችግሮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን ዜጎች ባለፉት አመታት በርካታ የትምህርት እድል ሲሰጥ መቆየቱን አንስተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ተወዳዳሪ፣ ብቁ እና ክህሎት ያላቸውን ተማሪዎች ለማፍራት እየሰራቸው ያሉ ሪፎርሞችን ለሉካን ቡድኑ ያብራሩ ሲሆን የነጻ የትምህርት እድል የተሰጣቸው ተማሪዎችም ሲመረጡ ይህንን ታሳቢ ያደርጉ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
በተለይም የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተናን እንዲሁም የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተናን እንደሚወስዱ አውቀው ሲመረጡ ይህንን ታሳቢ በማድረግ ጠንካራ መግቢያ ፈተና መስጠት እንዳለባቸውና ተማሪዎች ትምህርታቸውን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባቸውም አብራርተዋል።
የደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ትምህርት ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ክቡር ገብሬላ ቻንግሰን በበኩላቸው ከሁለት ዓመት በፊት የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት በጥሩ ሁኔታ እየተፈጸመ መሆኑን ገልጸው የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን ዜጎች በተሰጠው የነጻ ትምህርት እድልና እየተደረገላቸው ባለው ድጋፍ የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብን አመስግነዋል።
አክለውም ኢትዮጵያ ጥራትና ብቃት ያላቸውን ተማሪዎች ለማፍራት እየሰራች ያለውን ሥራ አድንቀው በደቡብ ሱዳንም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ጠንካራ እንዲሆን በማድረግ በኢትዮጵያ የትምህርት እድል የሚሰጣቸው ተማሪዎችም የተሻለ ውጤትና ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ እንሰራለን ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት ባደረጉት ውይይትም የትምህርት እድል የተሰጣቸው ተማሪዎች ከቪዛ፣ ከመኖሪያ፣ ከትራንስፖርት እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲ ቆይታ ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮችን መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳይ ላይ ከተወያዩ በኋላ የየድርሻቸውን ለመወጣት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ትምህርት ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ገብሬላ ቻንግሰን ቻንግ የተመራ ልዑክን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ዜጎች እየሰጠች ባለችው የትምህርት እድልና ባጋጠሙ ችግሮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን ዜጎች ባለፉት አመታት በርካታ የትምህርት እድል ሲሰጥ መቆየቱን አንስተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ተወዳዳሪ፣ ብቁ እና ክህሎት ያላቸውን ተማሪዎች ለማፍራት እየሰራቸው ያሉ ሪፎርሞችን ለሉካን ቡድኑ ያብራሩ ሲሆን የነጻ የትምህርት እድል የተሰጣቸው ተማሪዎችም ሲመረጡ ይህንን ታሳቢ ያደርጉ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
በተለይም የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተናን እንዲሁም የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተናን እንደሚወስዱ አውቀው ሲመረጡ ይህንን ታሳቢ በማድረግ ጠንካራ መግቢያ ፈተና መስጠት እንዳለባቸውና ተማሪዎች ትምህርታቸውን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባቸውም አብራርተዋል።
የደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ትምህርት ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ክቡር ገብሬላ ቻንግሰን በበኩላቸው ከሁለት ዓመት በፊት የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት በጥሩ ሁኔታ እየተፈጸመ መሆኑን ገልጸው የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን ዜጎች በተሰጠው የነጻ ትምህርት እድልና እየተደረገላቸው ባለው ድጋፍ የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብን አመስግነዋል።
አክለውም ኢትዮጵያ ጥራትና ብቃት ያላቸውን ተማሪዎች ለማፍራት እየሰራች ያለውን ሥራ አድንቀው በደቡብ ሱዳንም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ጠንካራ እንዲሆን በማድረግ በኢትዮጵያ የትምህርት እድል የሚሰጣቸው ተማሪዎችም የተሻለ ውጤትና ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ እንሰራለን ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት ባደረጉት ውይይትም የትምህርት እድል የተሰጣቸው ተማሪዎች ከቪዛ፣ ከመኖሪያ፣ ከትራንስፖርት እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲ ቆይታ ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮችን መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳይ ላይ ከተወያዩ በኋላ የየድርሻቸውን ለመወጣት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
Dec 16, 2024 399
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የጀኔራል ዋቁ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎበኙ።

ትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ የሚገኘውን ጀኔራል ዋቁ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸው ወቅትም ለተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርት የሚፈልገው ጥረት መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ተማሪዎች ጠንክረው መማርና ማጥናት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
በትምህርት ሥርዓቱ የፈተና አስተዳደር ስርዓቱን ማስተካከል ያስፈለገው የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ሀገር የሚረከቡ እውነተኛ ዜጎችን ለማፍራት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል።
ኩረጃ ለጊዜው የሚጠቅም ሊመስል ይችላል ነገር ግን ሄዶ ሄዶ ራስንም ሀገርንም ይጎዳል ያሉት ሚኒስትሩ ኩረጃን የሚጸየፉ በራሳቸው የሚሰሩና የሚተማመኑ ተማሪዎች መሆን እንዳለበቸውም አሳስበዋል።
የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ትውልዱ ይህችን ሀገር የመገንባት የወደፊት ሀላፊነቱን በታማኝነት እንዲወጣ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት በትምህርት ሴክተሩ እየተከናወኑ መሆኑንም አብራርዋል ።
አክለውም ነገ ብቁ ሀገር ተረካቢ ብሎም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ተማሪዎች ትምህርታቸው ላይ ብቻ አተኩረው እንዲማሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ የሚገኘውን ጀኔራል ዋቁ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸው ወቅትም ለተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርት የሚፈልገው ጥረት መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ተማሪዎች ጠንክረው መማርና ማጥናት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
በትምህርት ሥርዓቱ የፈተና አስተዳደር ስርዓቱን ማስተካከል ያስፈለገው የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ሀገር የሚረከቡ እውነተኛ ዜጎችን ለማፍራት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል።
ኩረጃ ለጊዜው የሚጠቅም ሊመስል ይችላል ነገር ግን ሄዶ ሄዶ ራስንም ሀገርንም ይጎዳል ያሉት ሚኒስትሩ ኩረጃን የሚጸየፉ በራሳቸው የሚሰሩና የሚተማመኑ ተማሪዎች መሆን እንዳለበቸውም አሳስበዋል።
የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ትውልዱ ይህችን ሀገር የመገንባት የወደፊት ሀላፊነቱን በታማኝነት እንዲወጣ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት በትምህርት ሴክተሩ እየተከናወኑ መሆኑንም አብራርዋል ።
አክለውም ነገ ብቁ ሀገር ተረካቢ ብሎም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ተማሪዎች ትምህርታቸው ላይ ብቻ አተኩረው እንዲማሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
Dec 13, 2024 348
Recent News
Follow Us